Saturday, 31 October 2020 11:29

የዶ/ር ደምስ ጫንያለው አዲስ መጽሐፍ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   ዶ/ር ደምስ ጫንያለው "ኢኮኖሚዉ፣ ፫ቱ ፖለቲከኞች እና ፖሊሲ"  በሚል ርዕስ ያሳተሙት አዲስ መጽሐፍ፤ ሕዳር 10 ቀን 2013 ዓ.ም በእለተ ሐሙስ፣ ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በፍሬንድሺፕ ኢንተርናሽናል ሆቴል  ይመረቃል።  
በምረቃ ሥነሥርዓቱ ላይ ከአዲሱ መጽሐፍ በተጨማሪ ዶ/ር ደምስ ቀደም ሲል በእንግሊዝኛ ያሳተሙት ‹‹The Quest for Change: Ethiopia’s Agriculture and Pastoral Policies, Strategies and Institutions; የተሰኘ መጽሐፋቸው ለሽያጭ እንደሚቀርብ ተጠቁሟል፡፡  
 ኢኮኖሚዉ፣ ፫ቱ ፖለቲከኞች እና ፖሊሲ፤ በ15 ምዕራፍ፣ መቅድሙን ጨምሮ 404 ገጽ  350 ብር፡፡ ሲሆን The Quest for Change: በ10 ምዕራፍ፣ መቅድሙን ጨምሮ 290 ገጽ 285 ብር ይቀርባል፡፡
ዛሬ ላይ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ አንፃር፣ ስለ ሶስተኛው ፖለቲከኛ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ይዘቱ፣ መገለጫውና ምንነቱ፣ እንዲሁም ይኸዉ ፖለቲከኛ በኢትዮጵያ ዉስጥ ስለሚጫወተው ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ሚና ማስገንዘቢያ እንዲሆን ከመጽሐፉ ምዕራፍ አምስት የተመረጡ አንቀፆችን በመንቀስ አባሪ ተደርጎ እንዲሰራጭ መደረጉንም ዶ/ር ደምስ ተናግረዋል፡፡  
ደራሲው ለአዲስ አድማስ በላኩት መግለጫ፤ "በምረቃው ዕለት መጥተዉ መጽሐፉን ይግዙ። በምዕራፍ አምስት ከተገለፀው በተጨማሪ በፖሊሲም ሆነ በተለያዩ ኢኮኖሚና ማሕበራዊ ልማት ጉዳዮች በርካታ ትምህርታዊ ማስረጃዎችና ማብራሪያዎችን ያገኙበታል፡፡" ሲሉ የግብዣ ጥሪ አድርገዋል፡፡  

Read 11419 times