Wednesday, 28 October 2020 00:00

ሮቦቶች የ85 ሚሊዮን ሰዎችን ስራ ሊነጥቁ ይችላሉ ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የሰው ልጅ እስከ መጪዎቹ አምስት አመታት ድረስ ለረጅም ዘመናት ሲያከናውናቸው ከኖራቸው የስራ አይነቶች መካከል ግማሽ ያህሉን የዘመኑ ቴክኖሎጂ ባፈራቸው ማሽነሪዎችና ሮቦቶች ይነጠቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተነግሯል፡፡
የአለም የኢኮኖሚ ፎረም ከሰሞኑ ባወጣው አለማቀፍ መረጃ እንዳለው፣ አለምን እያጥለቀለቀ ያለው የ“ሮቦቶች አብዮት”፤ የሰውን ልጅ ከስራ ገበታው በማፈናቀል ረገድ ተጽዕኖው እየተባባሰ እንደሚሄድና እ.ኤ.አ እስከ 2025 ወደ 85 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን ለስራ አጥነት ይዳርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በመላው አለም በሚገኙና እስከ 8 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰራተኞች ባላቸው 300 ታላላቅ ኩባንያዎች የሰራውን ጥናት ጠቅሶ ተቋሙ እንዳለው፣ አብዛኞቹ ኩባንያዎች ሰዎችን በሮቦቶች ለመተካት ማቀዳቸውን የተናገሩ ሲሆን ሮቦቶች የሰዎችን ስራ በከፍተኛ መጠን ይነጥቋቸዋል ተብለው ከሚጠበቁ የስራ መስኮች መካከልም የአስተዳደርና የመረጃ ማጠናከር መስኮች ይገኙበታል፡፡
በአሁኑ ወቅት በመላው አለም ከሚገኙት የስራ መስኮች መካከል ከ33 በመቶ በላይ የሚሆኑት በማሽኖችና ሮቦቶች ተይዘው እንደሚገኙ የጠቆመው ተቋሙ፣ በመጪዎቹ አምስት አመታት ግን ሮቦቶች በርካታ ስራዎችን ከሰዎች ይነጥቃሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክቷል፡፡


Read 2850 times