ሴቭ ዩር ጀነሬሽን ኢትዮጵያ ከዩኒሴፍ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የፎቶ አውደርእይ ትናንት በአሊያንስ ኢትዮፍራንስ የተከፈተ ሲሆን ይፋዊ መክፈቻውም ነገ ከጧቱ አራት ሰዓት በተመሣሣይ ስፍራ ይሆናል፡፡ ድርጅቶቹ በኦሮሚያ፣ አማራ፣ አዲስ አበባ እና ትግራይ ክልሎች ከሚገኙ ወጣት ማዕከላት በመውሰድ ያሰለጠኗቸው ወጣቶች በሥልጠናው ሂደት ያነሷቸውን ፎቶግራፎች እና የአንድ ደቂቃ ፊልም በአውደርእዩ ያሳያሉ፡፡ አውደርእዩ እስከ ሐምሌ 24 ለሕዝብ ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡