የግዕዝና አማርኛ ትርጉም ከአንድምታ ማብራሪያ ጋር ያካተተው “መጽሐፈ ሔኖክ” ሰሞኑን ለአንባቢያን ቀርቧል፡፡ በአባይነህ አስፋው የተዘጋጀው የጥንታዊው መጽሐፈ ሔኖክ የግዕዝና አማርኛ ትርጉም መሳ ለመሳ ከእነ አንድምታ ትርጉሙ የቀረበበት ነው ተብሏል፡፡
“መጽሐፈ ሔኖክ” በአለም ላይ በርካታ ምርምሮች እየተደረጉባቸው ካሉና በቁፋሮ ከተገኙ ጥንታዊ ቅዱሳት መጽሐፍ መካከል ተጠቃሽ ነው፡፡ በ584 ገፆች የተቀነበበው “መጽሐፈ ሔኖክ”፤በ203 ብር ለገበያ መቅረቡ ታውቋል፡፡