Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 28 July 2012 10:32

የዳንኤል ራድክሊፍ ሆረር ቅሬታ ፈጠረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በእንግሊዛዊው ወጣት ተዋናይ ዳንኤል ራድክሊፍ ተተውኖ ከወራት በፊት ለእይታ የበቃው  “ዘ ውመን ኢን ብላክ” የተሰኘው ፊልም አስፈሪነት በእንግሊዛውያን ላይ ቅሬታ መፍጠሩን ዴይሊ ቴሌግራፍ ዘገበ፡፡ በሆረር ፊልሙ ይዘት የተበሳጩ ከ120 በላይ እንግሊዛውያን ቤተሰቦች በብሪታኒያ የፊልም ደረጃዎች ምደባን ለሚሰራ ተቋም የቅሬታ ማመልከቻ ማስገባታቸውን የገለፀው ዴይሊ ቴሌግራፍ፤ በሃሪ ፖተር ፊልሞቹ ተወዳጅ የነበረውን ተዋናይ መውቀሳቸውን ጠቁሟል፡፡ ዳንኤል ራድክሊፍ የሃሪ ፖተር ፊልሞችን ከጨረሰ በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ የተወነበት “ዘ ዉመን ኢን ብላክ” የተባለ ሆረር ሲሆን ገቢው በዓለም ዙርያ 59.46 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነው፡፡

በዚሁ ፊልም ላይ ዳንኤል ጠበቃ ሆኖ የሚተውን ሲሆን ሁለት ህፃናት በአንዲት የሙት መንፈስ ራሳቸውን እንዲገድሉ ሲገፋፉ የሚተርክ ነው፡፡በሃሪ ፖተር ፊልሞቹ እጅግ ዝነኛ የሆነው ዳንኤል ራድክሊፍ፤ ሰሞኑን 23ኛ ዓመት ልደቱን ሲያከብር “ኤፍ ዎርድ” በተባለ የሮማንቲክ ኮሜዲ  እና  “ሆርንስ” በተሰኘ የፋንታሲ ፊልሞች  ለመተወን ስምምነት ላይ መድረሱ ይፋ ሆኗል፡፡ በትወና ሙያው 12 ዓመታት ያስቆጠረው ዳንኤል ራድክሊፍ፤ ከ11 ዓመቱ ጀምሮ በተወነባቸው ስምንት ሃሪፖተር ፊልሞች 70 ሚሊዮን ዶላር አግኝቷል፡፡ ባይ ዘ ነምበርስ የተባለው ድረገፅ በሰራው አሃዛዊ  ስሌት፤ ዳንኤል የሃሪፖተርን ፊልሞች ጨምሮ በተወነባቸው ከሃያ የማይበልጡ ፊልሞች በዓለም ዙርያ 7.80 ቢሊዮን ዶላር ያስገባ እና በሚሰራው አንድ ፊልም በአማካይ እስከ 223.42 ሚሊዮን ዶላር ማስገኘት የሚችል ምርጥ ወጣት ተዋናይ ነው፡፡

 

Read 1187 times