Wednesday, 16 September 2020 17:10

የአለም ባንክ ለኢትዮጵያ 80 ሚ. ዶላር ድጋፍ አደረገ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

የአለም ባንክ በኢትዮጵያ የግብርናውን ዘርፍ እድገት ለመደገፍና በአነስተኛ መሬት ለሚያርሱ ገበሬዎች የተሻለ አማራጭን ለመፍጠር የ80 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ማድረጉን ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቧል፡፡ የአለም ባንክ ስራ አስፈፃሚ ቦርድ የባንኩ አንድ አካል የሆነው አለም አቀፉ የልማት ማህበር፣ ለኢትዮጵያ 80 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ እንዲያደርግ በትናትናው ዕለት ውሳኔ አሳልፏል።ይህ ድጋፍ በዋነኝነት መንግስት የግብናውን ዘርፍ ምርታማነት ለማሻሻል የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ለመደገፍና በአነስተኛ መሬት የእርሻ ስራ ለሚያከናውኑ ገበሬዎች የገበያ እድል ለመፍጠር የሚውል ነው ተብሏል።

Read 5212 times