Thursday, 03 September 2020 00:00

ከፌስቡክ ገጾች በጨረፍታ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

የIQ ደረጃችን ሲበዛብን ነው!
                           (አንዷለም ቡኬቶ ገዳ)·


               ያው ዝምታው በዛ ብለን ተመለስናል!
ድንገት ከወራት ኩርፊያ በኋላ ወደ ቀየው ብዘልቅ፣ ወገኔ ሀገራችን በ IQ ደረጃ (የማንሰላሰል ልኬት) ከመጨረሻው ረድፍ አንዲት ሀገር ብቻ በልጣ በመገኘቷ፣ እንዴት ቢደፍሩን ነው እያለ ሲንጫጫ ደረስኩ!
ወገኞች!!
እንደው መለኪያው ያን ያህል አሳማኝ አይደለም እንጂ ከተወሰኑ አመታት ወዲህ ባለው አያያዛችን እንደውም አንዲት ሀገር እንኳን መብለጣችንስ እሰየው የሚያስብልስ አይደል?
እንደው በዚያ ሰሞን እንኳን የገዛ ወገኑን ገድሎ ቀኑን ሙሉ አስፓልት ላይ ሬሳውን እየጎተተ የሚጨፍር ሰው እያየን፣ ከሁለት አመት በፊት የመዋዕለ ህጻናት መምህር ለአመታት አብሯት የኖረውን ጎረቤቷን "ከክልሌ ውጣ" በሚል ጸብ ሬሳውን በክብሪት ለመለኮስ ስትጣጣር አይተን፣ ለምርምር የሄዱ ሃኪሞች እዚህ ግባ በማይባል ምክንያት በድንጋይ ተወግረው ሲገደሉ ታዝበን፣ የሚረባ የመጠጥ ውሃ እንኳን ያላቀረብንለትን ህብረተሰብ እንወክልሃለን የሚሉት ፖለቲከኞቻችን የሚከራከሩት ስለ መጠጥ ውሃ ማበልጸግ በተበጀተ ገንዘብ መጠን ሳይሆን የዛሬ ሁለት መቶ አመት ስለ ፈሰሰው የቅድመ አያቶቻቸው ደም መሆኑን እያየን እና በዚሁም የጅል ክርክር መነሻ ጠብታ ውሃ ያላፈሰሱለትን ድሃ ህዝብ ደም የሚያፈሱ ከንቱዎች መሆናቸውን ስናይ--- በአጠቃላይ አጠገቡ ሃምሳ አመት በጉርብትና ከኖረው የሌላ ቋንቋ ተናጋሪ ጎረቤቱ ይልቅ በህይወቱ አይቶት የማያውቀውን አምስት መቶ ኪሎ ሜትር ላይ የሚገኝ የሱን ቋንቋ የሚናገር ባእድ የሚያስበልጥ፣ ብሄሬ፣: ጎሳዬ፣ ህዝቤ ደሜ፣ ጎጤ ወዘተ እያለ ኢማጅንድ በሆነ ኮሚኒቲ ውስጥ እራሱን መድቦ ሲጠዛጠዝ የሚውል፣ 80 ምናምን ቡድን ይዘን...የአውሮፓ ሀገራት “ሀገር ምን ይሰራል?!” ብለው ወደ አንድ ለመሰባሰብ ሲጣጣሩ፣ እኛ በክልልና በወረዳ ፍቅር እየናወዝን ስንጫረስ ከርመን፣ ከከተማ ከተማ እንኳን በሰላም መንቀሳቀስ ተስኖን፣ የተፈጥሮ ጸጋ ሞልቶ በተረፋት ሀገር ላይ ተቀምጠን ተመጽዋች ሆነን የቀረን ህዝቦች፣ ከአለም አንደኛ ሀገር ተረክበን በጥቂት አመታት ውስጥ የአለም መጨረሻ ለማድረግ የተሳካልን የዘመን ጉዶች ...በውጤቱ ለምን ይሆን የሚከፋን?!
ደህና ከረማችሁ ግን?!ተናፍቃችኋል!

Read 5648 times