Thursday, 03 September 2020 00:00

እንግሊዝ በኢንተርኔት ፍጥነት አዲስ ክብረወሰን አስመዘገበች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በሰከንድ 178 ቴራባይት ፍጥነት አለው
 
        የእንግሊዙ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ለንደን ተመራማሪዎች በአለማችን የኢንተርኔት ፍጥነት አዲስ የአለም ክብረ ወሰን ያስመዘገቡበትንና በአንድ ሰከንድ 178 ቴራባይት መጠን ያለው መረጃ ማስተላለፍ የሚያስችለውን አዲስ የምርምር ውጤት ከሰሞኑ ይፋ ማድረጋቸው ተዘግቧል፡፡
ተመራማሪዎቹ ይፋ ያደረጉት የኢንተርኔት ፍጥነት ከዚህ በፊት በክብረ ወሰንነት ተይዞ ከነበረው የኢንተርኔት ፍጥነት በ20 በመቶ ያህል እንደሚበልጥ የጠቆመው የኢንዲፔንደንት ዘገባ፤በአንዲት ሰከንድ እጅግ በርካታ መጠን ያለውን መረጃ በማስተላለፍ አቻ እንደማይገኝለትም ገልጧል፡፡
በታዋቂው የኔትፍሊክስ ድረገጽ ላይ ያሉትን መረጃዎች በሙሉ በአንድ ሰከንድ ዳውንሎድ ማድረግ ያስችላል የተባለውን ይህንን ፈጣን የኢንተርኔት ኮኔክሽን ለመፍጠር፣ ከተለመዱት የተለዩና የተራቀቁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችንና አሰራሮችን መከተላቸውንም አክሎ ገልጧል፡፡ ተመራማሪዎቹ አዲስ የአለም ክብረ ወሰን ያስመዘገቡበትን የምርምር ስራ ለስኬት ያበቁት ኤክስቴራ እና ኬዲዲአይ ከተባለ የምርምር ተቋም ጋር በአጋርነት ባከናወኑት ፕሮጀክት መሆኑንም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 5466 times