Tuesday, 25 August 2020 05:14

ከፌስቡክ ገጾች በጨረፍታ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 የማከብረው
                    ቴዎድሮስ ፀጋዬ

            ይሄ ሰውዬ እጅግ ከማከብራቸው ቃለ-መጠይቅ አድራጊዎች መሀል ፊት መሪው ነው። ለቴዎድሮስ ፀጋዬ ቃሌን ስሰጥ በኩራት ነው።
ቴዲ ከሁሉም በላይ ኢትዮጵያ ውስጥ በነበረ ጊዜ ማንም ስለ ኢትዮጵያዊነት ሳይደፍር ደፍሮ ይሰራ ነበር። “አሁን የሚያነሳቸውን አጀንዳዎች ያኔ ሀገር ቤት እያለ ለምን አያነሳም ነበር?“ የሚሉ ተደጋጋሚ አስተያየቶች እሰማለሁ። ያን ጊዜ አለማወቅ ነው።
በመንግሥት የአየር ሰዓት እንኳን መስራት መሞከሩም ከስቱዲዮ አስጎትቶ ያስወስዳል። የመጣንበትን መንገድ መርሳት ይሆናል።
በተለይ ቃለመጠይቅን እንደ ቴዲ አድምቶ የሚሰራ አላውቅም። እንግዳውን ዛሬ ደውሎ ነገ ስቱዲዮ ይዞ የሚገባ አይደለም። ለአንዱ እንግዳ የሚያደርገው ዝግጅት እኔን ያደክመኛል። በሙያው ቀልድ አያውቅም። በትምህርት ዝግጅቱ የህግ ባለሙያ ቢሆንም፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ በስራዎቹ ራሱን ተፈላጊ ማድረግ የቻለ ብርቱ ሰው ነው።
በሙያ መዘሞትን አምርሮ ይጠላል። ገንዘብ እያስፈለገው እንኳ አንድም ጊዜ ስራው ብር ብር ሸቶኝ አያውቅም። ቴዲ ባለፈባቸው መንገዶች ለማለፍ የሞራል ድፍረት ያለው ራሱ "Tewodros_Tsegaye ብቻ ነው። ይህ ማለት ግን በቃለመጠይቆቹም ሆነ በሚያነሳቸው ሀሳቦች ሁሉ እስማማለሁ ማለት አይደለም። የምቃወማቸውም በዝምታ የማልፋቸውም ይኖሩኛል።
የእጅግ ብዙዎቹ ግን አድናቂ ነኝ። ማንንም ሰው ለማክበር ሀሳቡ እኔን መምሰል የለበትም። እኔ ያዘጋጀሁትን ድንጋይ ስለወረወረልኝ አይደለም ማንንም ሰው የማደንቀው። የቴዲ ሀገር ወዳድነት እንደ የገበያ ስራ አይደለም። ከልቡ ነው። ላመነበት ሀሳብ ችኮ ነው። አይጎናበስም። ግትር ነው። ሀሳቡ ብዙ ሊያስከፍለው እንደሚችል እያወቀም ይሄድበታል። ዋጋም ከፍሎበታል። የማስታወቂያ ገቢ ለፕሮግራሙና ለኑሮው እስትንፋስ መሆኑን እያወቀ ያመነበትን ሀሳብ በማንሳቱ ገቢውን ሲያስቀር አውቃለሁ። አይደንቀውም።
ወዳጄ ቴዲ፤ ስላየሁህ ደስ ብሎኛል። በአካል ወይም በነፍስ የምንገናኝበት ጊዜ ይመጣል።


Read 1508 times