Monday, 17 August 2020 00:00

የ19 አመቱ ኡጋንዳዊ ታዳጊ ለፕሬዚዳንትነት ሊወዳደር ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ሂላሪ ሃምፍሬ ካዌሳ የተባለው ኡጋንዳዊ የ19 አመት ታዳጊ በመጪው የአገሪቱ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ለመወዳደርና አገሪቱን ከ35 አመታት በላይ ያስተዳደሩትን ሙሴቬኒን ለመተካት ዝግጅት ማድረግ መጀመሩን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
አገር አልምራ እንጂ ወትሮም የመሪነት ብቃት አለኝ፤ አገሬን ለመምራት ብቁ ነኝ የሚለው ካዌሳ፣ ለዕጩ ተወዳዳሪነት ምዝገባ ክፍያ የሚያስፈልገውን 5ሺህ 400 ዶላር ከለጋሾች ለማሰባሰብ መዘጋጀቱን ማስታወቁን የጠቆመው ዘገባው፣ ከ100 በላይ የአገሪቱ ግዛቶች ከእያንዳንዳቸው 100 የድጋፍ ፊርማ ለማሰባሰብ ማቀዱንም አመልክቷል፡፡
በአገሪቱ ህገ መንግስት መሰረት ዕድሜው ከ18 አመት በላይ የሆነው ዜጋ ለፕሬዚዳንትነት መወዳደር እንደሚችል የጠቆመው ዘገባው፣ ታዳጊው ኡጋንዳን ከሶስት አስርት አመታት በላይ በብቸኝነት ያስተዳደሩትንና አሁንም ስልጣናቸውን ለማራዘም ቆርጠው የተነሱትን ፕሬዚዳንት ዩሪ ሙሴቬኒን ተክቶ አገሪቱን በአዲስና በትኩስ ሃይል ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር ቆርጦ መነሳቱን እንደገለጸም አክሎ ገልጧል፡፡


Read 2721 times