Sunday, 09 August 2020 00:00

ኮሮና በአለማችን ከ1 ቢሊዮን በላይ ተማሪዎችን ተጎጂ አድርጓል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በመላው አለም ከ1 ቢሊዮን በላይ የሚሆኑ ተማሪዎችን ተጎጂ ማድረጉን የገለጹት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ አለማችን ከኮሮና ጋር በተያያዘ ትምህርት ቤቶች በመዘጋታቸው ምክንያት የከፋ አጠቃላይ ቀውስ ሊገጥማት እንደሚችል አስጠንቅቀዋል፡፡
በአለም ዙሪያ በሚገኙ ከ160 በላይ አገራት ከኮሮና ስጋት ጋር በተያያዘ ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውንና በዚህም ከአንድ ቢሊዮን በላይ ተማሪዎች ተጎጂ መሆናቸውን የጠቆሙት ጉቴሬዝ፣ ወረርሽኙ ከመከሰቱ በፊትም 250 ሚሊዮን ያህል የአለማችን ህጻናት ከትምህርት ገበታ ውጪ እንደነበሩ ማስታወሳቸውንም ሮይተርስ ዘግቧል።
የአለማችን አገራት መንግስታት ወረርሽኙን በቁጥጥር ስር ካዋሉ በኋላ ቅድሚያ ሊሰጡት የሚገባው አንገብጋቢ ጉዳይ ተዘግተው የቆዩ ትምህርት ቤቶችን መክፈት መሆኑን ዋና ጸሃፊው ባለፈው ረቡዕ በሰጡት መግለጫ መናገራቸውንም ዘገባው ገልጧል፡፡


Read 1923 times