በርካታ መንፈሳዊና ማህበራዊ የህትመት ውጤቶችን አትሞ በማሠራጨት የሚታወቀው ትንሣዔ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት አዲስ ህንፃ ሊያስገነባ ነው፡፡ አምስት ኪሎ ጠቅላይ ቤተክህነት አካባቢ በ3ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ለሚሠራው ህንፃ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክርስቲያን አንድ መቶ ሃያ ሚሊዬን ብር የመደበች ሲሆን ከትላንት ወዲያ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትሪያሪክ አቡነጳውሎስ የመሠረት ድንጋይ አኑረዋል፡፡ በስነስርዓቱም ላይ ህዝበ ክርስቲያኑን ጨምሮ ኢትዮጵያውያን ሊቃነጳጳሳትና የምስራቅ ኦርቶዶክስ ሌሎች ጳጳሳት ተገኝተዋል፡፡