በትሩዝ ፊልም ፕሮዳክሽን የተዘጋጀው እና በደራሲ መሐመድ ዳውድ ተደርሶ በዘሪሁን አስማማው እና በሳሙኤል ደበበ ዳሬክተርነት የተሠራው “አየሁሽ” ፊልም በነገው ዕለት በአዲስ አበባና በክልል ሲኒማ ቤቶች በ8፡00፣ በ10፡00 እና በ12፡00 ሰአት የሚመረቅ ሲሆን በልዩ ፕሮግራም በሀርመኒ ሆቴል ጥሪ የተደረገላቸው ሚኒስትሮች፣ አምበሳደሮች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አርቲስቶች እና ጋዜጠኞች በተገኙበት እንደሚመረቅም ታውቋል፡፡ ፊልሙ የፍቅር ኮሜዲ ይዘት ያለው ሲሆን የ1፡30 ርዝመት እንዳለውና ሠርቶ ለማጠናቀቅ ስምንት ወር እንደፈጀ አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡