Print this page
Sunday, 19 July 2020 00:00

"እያንዳንዱ ስኬት የጊዜ መስዋዕትነት ውጤት ነው"

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 አዜብ ወርቁ ፀሐፌ ተውኔት፣ ተርጓሚ፣ ተዋናይት፣ መምህርት፣ ጋዜጠኛና  መድረክ መሪ ናት፡፡ በአሁኑ ወቅት የአርትስ ቴሌቪዥን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆናም በመስራት ላይ ትገኛለች፡፡ በቅርቡ ‹‹እረኛው ሐኪም›› የተሰኘ መፅሐፍ ከፈረንሳይኛ ወደ አማርኛ መልሳ ለንባብ አብቅታለች፡፡ ስምንቱ ሴቶች የተሰኘ ቴያትርን ከፈረንሳይኛ ወደ አማርኛ ተርጉማ በዳይሬክተርነት ለዕይታ አብቅታለች፡፡ የ#ዳና; እና  "ገመና 2" ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ደራሲም ናት፡፡ የአዲስ አድማስ አምደኛ ደረጀ በላይነህ በመጽሐፏ፣ በሕይወቷ፣ በጥበብ ፍልስፍናዋና በሙያዋ ዙሪያ አነጋግሯታል፡፡ እነሆ፡-


             በተመሳሳይ እድሜ ላይ ብንገኝ ወይም የአንድ ቤተሰብ አካል ብንሆንም፤ በቁመታችን በመልካችን፣ በጉልበታችን፣ በእምነታችን፣ በመንፈሳችንና በአስተሳሰባችን እንለያያለን፡፡ በልዩነታችን ውስጥ ግን ታላቅ የአንድነት ሃይል አለ፡፡ ሃይላችን ሁላችንም እግዜርን መምሰላችን ነው፡፡ “በመልኬ ፈጥሬአችኋአለሁ” ብሏልና:: እግዜር ማለት ሁለንተናዊ ተፈጥሮ ማለት ነው…ምዕሉ በኩልከ!!
ወዳጄ፡- አንድ አጭር ሰው በረዣዥሞች ወይም ረዥም ሰው በአጫጭሮች መሃል ሲገኝ ምቾት ካልተሰማው ተፈጥሮን አልተረዳትም፡፡ አጭሩ እንደ ለንቋሳ ማሽላ ፍሬ ለወፍ ወይም ለወንጭፍ ቀድሞ ሲሳይ አይሆንም፡፡ ረዥሙ ደግሞ የሞላ ኩሬን ተዘናክቶ ሊያቋርጥ ወይም ከበለሷ ጫፍ ላይ የተንጠለጠሉትን በለስ ፍሬዎች በቀላሉ ሊያወርዳቸው ይችላል፡፡ ሁለቱም የየራሳቸው ፀጋ አላቸው፡፡የቁመት ነገርን ካነሳን፣ አንድ የድሮ አማርኛ ተረት መጽሐፍ ላይ “ፍርደ ገምድል ዳኛ“ የሚል ታሪክ አለ፡-
ተምትም የተባለው ሰው ባጠፋው ጥፋት በስቅላት እንዲሞት ይፈረድበታል:: አስፈፃሚዎቹ ፍርዱን ለመተግበር ወደ መግደያው ቦታ ሲወስዱት የሰውየው ቁመት ከመስቀያው እኩል ሆነና ተቸገሩ:: ወደ ንጉሱ ተመልሰው ያጋጠማቸውን ሲነግሩት፤ “ከዘመዶቹ መሃል አጭር የሆነውን መርጣችሁ ስቀሉ“ አላቸው:: ቁመት ዠርጋጋው ተምትምን ሲያድን፣ ምንም ያላጠፋውን ዘመዱን ደግሞ ሞት አስፈረደበት፡፡ እንደ ንጉስ ዳዊት ብልህ የሆኑ አጫጭር ታሪኮችም ሞልተዋል፡፡
ወዳጄ፡- ሰዎች በአካልም ሆነ በአእምሮ የተባረኩበት ግለሰብአዊ ፀጋ አላቸው:: ችሎታ ወይም ብቃት የምንለው ሃይል ከዚህ ፀጋ ይመነጫል፡፡ ከትንኝ ጀምሮ እስከ ትልቁ እንስሳ ድረስ በዚህ “መክሊት“ ተክህኖ አለው፡፡ የታንኳ ቀዛፊው ብላቴናና በታንኳ ላይ ተሳፍረው የነበሩትን ፕሮፌሰር  ጨዋታ ቀንጭበን እናስታውሳለን፡-
“ወዳጄ ተምረሃል?“
“አረ በጭራሽ“
“እንደው ምንም?“
“ምንም“
“አዝናለሁ“ አሉ ፕሮፌሰሩ ከልባቸው:: …ሁለቱ ሰዎች እየተንሸራሸሩ ሲጫወቱ አያድርስ እንደሚባለው ሆነና ሃይቁ በማእበል ተመታ፤ታንኳቸው ራደች፡፡ ምስኪኑ ቀዛፊ ተደናግጦ ፕሮፌሰሩን፡-
“ዋና ይችላሉ?" በማለት ጠየቃቸው።
“አረ በጭራሽ!"
“እንደው ምንም"  
“ምንም"
“አዝናለሁ" አለ በልቡ፤ የማዕበሉን መክፋት አይቶ፡፡ ከዛ በኋላ የሆነውን አስቡት፡፡ ዲተርሚኒስቶች ሁለቱም ተረቶች በህይወት መዝገብ ላይ እንደተጻፈው የተከናወኑ ናቸው ይሉናል፡፡ አንተ ምን ትላለህ?
ወዳጄ፡- ተረግሞ ወይም ተመርቆ የተፈጠረ ማንም የለም፡፡ ዕርግማንና ምርቃት የራስን ፀጋ የመረዳት፤ የራስን ማንነት የመቀበል ወይም በተቃራኒው የማሰብ ጉዳይ ነው፡፡ የራስን ጸጋ አለማወቅ በሌላው ላይ የመቅናት ስሜት ያሳድራል:: ቅናት የተፈጥሯችን አካል ነው፡፡ ፈጣሪ እንኳን “እኔ ቀናተኛ አምላክ ነኝ" ማለቱ ተፅፏል፡፡ ቅናት እርግማን የሚሆነው ወይም ጥፋት የሚያስከትለው እራሳችንን ስናሳንስ ወይም የበታችነት ስሜት በውስጣችን ሲያቆጠቁጥ ነው፡፡ ቃየል በወንድሙ ላይ የተነሳሳው እራሱን ዝቅ አድርጎ ስለገመተ ነበር፡፡
ወዳጄ፡- የዝቅተኝነት መንፈስ አጉል ቅናት ይወልዳል ያልነው ያለ ምክንያት አይደለም:: አጉል ቅናት ጥላቻን፤ ጥላቻ ደግሞ ጥፋትን ያስከትላል፡፡ በራሱ የሚተማመን ሰው አይቀናም፡፡ በራሱ የሚተማመን ሰው እሱ የሌለውን ወይም ያጣውን፤ ሌሎች የተቀበሉትን ወይም ያላቸውን እየመረመረ፤ እየመዘነ ይማርበታል፡፡ ተበለጥኩኝ በሚል ቅዠት ሌላውን ማጥላላት አላዋቂነት ነው፡፡
ህውሃት በተሰነጠቀበት “ገማን፣ በሰበስን፣ ቦናፓርቲዝም ምናምን" በተባለበት ሰሞን የታዘብነው የቅናት ፖለቲካ ቦታውን ቀይሮ ዛሬ ላይ የተቀናባቸው ሲቀኑ፣ ታሪክ እራሱን ሲደግም ማየት ያስገርማል፡፡ የቅናት ፖለቲካ የወጡበትን የወረዱበትን ትግልና ጓዳዊነት፣ ጎን ለጐን ሆነው የተዋጉለትን ዓላማና አንድነት በአንድ አረፍተ ነገር ዜሮ ድምር ያደርገዋል፡፡ ይህ ጉዳይ በህወሃት ብቻ ሳይሆን በኢህአፓ፣ በመኢሶን፣ በቅንጅት፣ በኦነግ፣ በመኢአድ፣ በአንድነት፣ በኢዴፓ፣ በኦብኮ፣ በኢህአዴግና በሌሎች የፖለቲካ ፓርታዎችና እንደ መምህራን ማህበር በመሳሰሉት የሙያ ማህበራት ውስጥ ተከስቷል፡፡
መለስ ዜናዊ ላይ የቀረበው ክስ ሃሳብን በተሻለ ሃሳብ መሞገትን መሰረት ያደረገ አልነበረም። በዘርና በቅናት የተቃኘ የቅናት ፖለቲካ እንደነበር የወቅቱ ምክትል ጠ/ሚኒስትር አቶ አዲሱ ለገሰ ሲናገሩ አድምጠናል። መለስም በብሔራዊ ቴሌቪዥን ቀርበው በዋልታ ኢንፎርሜሽን ድርጅት ስራ አስኪያጅ በነበሩት አቶ ሴኩ ቱሬ ጠያቂነት፡-
’’´ተቀናቃኞች ኤርትራዊ ነዎት እያሉ ነው፤ ምን ይላሉ?’’ ሲባሉ
’’ጥያቄው ማን ምንድን ነው ሳይሆን ማን ምን ሰራ ነው? መሆን ያለበት’’ በማለት  ነበር  የመለሱት፡፡ እንደ  ምሳሌም ጠያቂያቸውን ራሱን፡-
"’አንተ አማራ ነህ፤ ነገር ግን የህወሐት አባል ነህ’’ በማለት ሰዎችን የሚያጸናቸው የዘርና የጎሳ ትስስር ሳይሆን የአላማ አንድነት እንደሆነ ለማስረዳት ሞክረዋል። ይኽውም የጎሳ ፖለቲካ ፉርሽ እንደሆነ በአንደበታቸው የመሰከሩበት አጋጣሚ ነበር። በተግባር አላየነውም እንጂ። በነገራችን ላይ ጥራት በሌለው ትምህርትና አጓጉል ሰርተፍኬቶች አገራችን በታጠነችው ቅናት የወለደው ፖለቲካ ሰበብ አላማችንን እስተቀበለ ድረስ ዘበኛም ቢሆን ሚኒስትር ሊሆን ይችላል ያሉትን ለማካካስ ታስቦ የተደረገ በመሆኑ ነው።
ወዳጄ፡-
ኢትዮጵያውያንን የሚያስጨንቃቸው መሪዎቻቸው የወጡበት ጎሳ ወይም ክልል ወይም ቤተሰብ አይደለም። ኢትዮጵያውያን የሚፈልጉት አድሎ የሌለበት አስተዳደር ነው። የፍትህ ስርአቱን በብቃት የሚያስፈፅሙለትን ሰዎች ነው። መሪዎች እንደ ፖለቲከኛ ለሀገራቸው ሰላም፤ አንድነትና ብልፅግና፣ ጥቅም የሚያስገኝ ዲፕሎማሲያዊ ትግል ካደረጉ፣ እንደ ምሁር ለሳይንስና ለጥበብ ዕድገት መሰረት የሚጥል የትምህርት ስርዓት በማደራጀት የስልጣኔ ፋና ወጊዎችን ካፈሩ፤ እንደ ግለሰብ እርህሩህና የተፈጥሮ ወዳጅ ከሆኑ በቂ ነው።
ወዳጄ፡- አንድ ነገር ልብ በል። “ግለሰቦች ራሳቸውን ይሰራሉ፤ መሪዎችን ግን ህዝብ ይሰራቸዋል ይባላል። ከመልካም ህዝብ ውስጥ መልካም፣ ከሰራተኛ ህዝብ ውስጥ ሠራተኛ፣ ከጀግና ህዝብ ውስጥ ጀግና፣ ከሰለጠነ ህዝብ ውስጥ የሰለጠነ መሪ ይወጣል። ነገር ግን ሁሉም ሕዝብ በአንድ ጊዜ መልካም፣ ሰራተኛ፣ ጀግና፣ የሰለጠነ ሊሆን አይችልም። መሪ ግን ሁሉንም በመሆን ያስተባብራል። ይህን ችሎታና ታጋሽነት ነው የቃለ አብነት ፀጋ (wisdom) የምንለው።
ወዳጄ፡- እያንዳንዱ ሰው የራሱ ብርሃን፣ የራሱ ጨለማ እና ንጋት አለው። መስታወት ፊት የቆመች ድመት የነብር ፊት ከታያት ወይም የተገላቢጦሽ ከሆነ ቅዠት ነው። እራስን ያለ ቦታ ማስበለጥም ሆነ ማሳነስ ተፈጥሯዊ ፀጋን አለመረዳት ይሆናል። ሰዎች ታሪካቸውን የሚሰሩት እራሳቸው በመረጡት መስመር አይደለም። እንደውም ተከታታይነት ያላቸው ሁኔታዎችና የመጡበት ኮሮኮንች መንገድ ነው ሰዎቹን የሚሰራቸው ይባላል። “Men could make their own history, but not under circumstances chosen by themselves, but under the circumstances encountered, given and transmitted from the past” ይላል ካርል ማርክስ፤ The 18th brumier of laos Bonaparte በሚለው መፅሐፉ፡፡
ወቅታዊ ጉዳዮች ስናተኩር የአባይ ግድብ ከትላንት ወዲያ ጀምሮ ውሃ ለመሙላት እንደጀመረ የሳተላይት ምስሎች እንደሚያሳየው ከአሜሪካን ድምፅ ሬድዮ ሰምተናል። እንደዚሁም በሚቀጥሉት ዓመታት ሀገራችን ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት እንደምታስመዘግብ የሚያረጋግጡ ጥናቶች እየወጡ መሆናቸው ተነግሯል። ወዳጄ፡- ኢትዮጵያ አትቆምም!!
እንዲሁም በዓለም ላይ አለ ብዙ ነገር
በዚህ ቢሉት በዚያ መሆኑ የማይቀር --- ይሉናል ከበደ ሚካኤል። በዚህም ቢሉን በዚያ ወደ ኋላ አንመለስም።
“ኑ! መስቀሉን የተሸከመውን እናግዝ" የሚለን ደግሞ ዶስቶቪይስኪ ነው… እንደ ቤን ኸር!!

Read 1601 times
Administrator

Latest from Administrator