የማይነጋ ምሽት
በዚህ ሃገር ሰማይ
ጨረቃ የለችም
ወይም ተሰዳለች
አሊያም ከናካቴው አልተፈጠረችም።
በዚህ ሃገር ሰማይ
ከዋክብትም የሉም
በብርሃናቸው፤ ሰማይ አያስጌጡም፡፡
ሰማዩም መልክ የለው
ያገሬን አይመስል
ፀሃይ ትበርዳለች
በግዜ ይመሻል።
በዚህ ሃገር ሰማይ
ወፎችም አይበሩም
በጥዑም ድምፃቸው
ንጋት አያበስሩም።
(ለውብ የሃገሬ ምሽት፤ ከባህር ማዶ)
Published in
የግጥም ጥግ
የማይነጋ ምሽት
በዚህ ሃገር ሰማይ
ጨረቃ የለችም
ወይም ተሰዳለች
አሊያም ከናካቴው አልተፈጠረችም።
በዚህ ሃገር ሰማይ
ከዋክብትም የሉም
በብርሃናቸው፤ ሰማይ አያስጌጡም፡፡
ሰማዩም መልክ የለው
ያገሬን አይመስል
ፀሃይ ትበርዳለች
በግዜ ይመሻል።
በዚህ ሃገር ሰማይ
ወፎችም አይበሩም
በጥዑም ድምፃቸው
ንጋት አያበስሩም።
(ለውብ የሃገሬ ምሽት፤ ከባህር ማዶ)