የኢትዮጵያ ፌዴራሊስት ኃይሎች ጥምረት፣ ህወሓትና የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ሕብረትን (ኢዴሕ) ከጥምረቱ መተዳደሪያ ደንብ ውጪ ሆነው ተገኝተዋል በሚል ከአባልነት መሰረዙን አስታወቀ። ጥምረቱ ይህን ያስታወቀው አራተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በአዲስ አበባ ካካሄደ በኋላ በሰጠው መግለጫ ነው፡፡
ጥምረቱ በአደረጃጀቱ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ማድረጉን የጠቆመ ሲሆን የአገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታና የጥምረቱ ቀጣይ አቅጣጫ ላይ መወያየቱንም አስታውቋል፡፡ በዚህም ውይይት ላይ ጥምረቱ.፤ ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ጥምረቱ ውስጥ ወዥንብር እየፈጠረ ነው ሲል ወቅሷል፡፡
የጥምረቱ የአደረጃጀት ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ቶሎሳ ተስፋዬ እንደገለጹት፤ “ፓርቲው የጥምረቱ አባላትን ለመከፋፈል የተለያዩ ጫናዎች እየፈጠረ ነው” ሲሉ ወንጅለዋል፡፡
ህወሓት ከዚህም ባሻገር፣ ጥምረቱን እንደ ሽፋን ተጠቅሞ፣ አገርን ለማወክ እየተንቀሳቀሰ ነው ብለዋል፤ሰብሳቢው በመግለጫቸው፡፡ በተጨማሪም ፓርቲው በጥምረቱ ስብሰባ ላይ እንደማይገኝና የጥምረቱ ስብሰባም መቀሌ ካልተካሄደ ተቀባይነት እንደሌለው እየገለጸ ነው ሲሉ ከስሰዋል።
“ህወሓት እኔ ያልኩት ካልሆነና እኛ ካልመራን ትክክል አይደለም; የሚል ግትር አቋም ያራምዳል ሲሉም ነቅፈዋል፡፡
የጥምረቱ ሊቀ መንበር አቶ ደረጄ በቀለ እንደሚሉት፤ ህወሓትና ኢዴሕ፣ ሕገ ወጥ በሆነ መልኩ እየተንቀሳቀሱ በመሆኑ ታግደዋል፤ ይህንንም ሁሉም የጥምረቱ አባላት የተስማሙበት ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡
“በተለይ ህወሓት 6ኛው ብሔራዊ ምርጫ ተራዝሞ ሳለ ለጥምረቱ ሳያሳውቅ ምርጫ አካሂዳለሁ; ማለቱ የህገ ወጥነቱ ማሳያ ነው ብለዋል፤ሊቀ መንበሩ፡፡
ጥምረቱ 24 ፓርቲዎችን ያቀፈ ሲሆን በትናንቱ ጉባኤው 22 የፖለቲካ ፓርቲዎች ተገኝተዋል፤ ሌሎች አምስት የፖለቲካ ፓርቲዎችም ጥምረቱን መቀላቀላቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
Published in
ዜና
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል