Monday, 20 April 2020 00:00

የዛሬ መራራቅ ነገ ያቀራርበናል!

Written by  ትዕግስቱ በለጠ
Rate this item
(3 votes)

ወገኖቼ፤የምንተርፈውም የምንጠፋውም ተያይዘን ነው፡፡ ‹‹ጨው ለራስህ ስትል ጣፍጥ፤ አለበለዚያ ድንጋይ ነው ብለው ይጥሉሃል›› የሚለው አገራዊ ብሂል፣ ለኮሮና ቫይረስ አይሰራም፡፡ ካልጣፈጥን ሁላችንም ነን ተያይዘን የምንጣለው፡፡ (ልብ በሉ፤ እስካሁን በመላው ዓለም ከ2 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን ከ120 ሺ በላይም በበሽታው ህይወታቸው አልፏል፡፡)
እና ምን ይሻላል? በፍጥነት ከዝንጋታ እንውጣ፡፡ ከእንቅልፋችን እንንቃ!! ለምንወዳቸው ቤተሰቦቻችን ስንል አካላዊ ርቀት መጠበቅን ጨምሮ ሁሉንም የመከላከያ ጥንቃቄዎች ሳንዘነጋ እናድርግ፡፡ ነገ ከመጸጸት ዛሬን በአስተውሎት እንጓዝ፡፡ ለሞት ከሚዳርግ ክፉ ወረርሽኝ ጋር ጦርነት መግጠማችንን ተገንዝበን፣ በቆራጥነትና በጀግንነት ውጊያችንን እናፋፍም፡፡ ከኛ የሚጠበቀው ጥንቃቄ ብቻ ነው፡፡
ልብ በሉ፤  የዛሬ መራራቅ ነገ ያቀራርበናል:: የዛሬ አለመጨባበጥ ነገ ያስተቃቅፈናል፡፡

Read 2783 times