Saturday, 28 March 2020 11:54

የኮሮና ቫይረስ መድሃኒት በሙከራ ላይ እንደሆነ ተገለጸ

Written by 
Rate this item
(11 votes)

   የኮሮና ቫይረስን በሳይንሳዊ ምርምር በተደገፈ የሀገር በቀል እውቀት ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር በማቀናጀት፣ ቫይረሱን ለማከም የተሰራው መድሃኒት መሰረታዊ የምርምር ሂደት በማለፍ ተደጋጋሚ የቤተ ሙከራ ሞዴሊንግ ሂደቶችን በስኬት ማለፉ ተገልጿል፡፡
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር እንዳስታወቀው፤ ምርምሩ የኮሮና ቫይረስ በዓለም ላይ መከሰቱ ከተሰማ ጊዜ ጀምሮ ከተለያዩ በሃገር ውስጥና ከሃገር ውጪ ከሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር በመሆን ሲካሄድ የቆየ ሲሆን ተደጋጋሚ የምርመር ሂደት አልፎ ወደ ምርትና ቀጣይ የእንስሳት ፍተሻና ክሊኒካል ፍተሻ ስራዎች እንዲሸጋገር ተደርጓል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር ኢንጂ.)፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ፣ ከኢትዮጵያዊያን የባህል ሃኪሞችና የህክምና ተመራማሪዎች ጋር በመሆን የሀገር በቀል እውቀቶችን በሳይንሳዊ ሂደቶች በማሳለፍ፣ ለዘመን አመጣሹ ኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ - 19) ወረርሽኝ ህክምና የተዘጋጀውን መድሃኒት ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችላቸውን ስራ በመስራት ላይ ይገኛሉ።
መድሃኒቱ የመከላከል አቅም የሚጨምር፣ መርዛማነት የሌለውና አዋጭነቱ የተረጋገጠ እንደሆነም ተገልጿል፡፡


Read 15307 times