ይህ በዚህ እንዳለ ቢፈዋቃ ፊልሞች “ሄሉ ኢትዮጵያ” የተሰኘ አዲስ ልብ አንጠልጣይና ማህበራዊ ሕይወትን የሚያሳይ ፊልም ነገ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ በሚገኘው ሐርመኒ ኢንተርናሽናል ሆቴል ያስመርቃል፡፡ ዮሐንስ ፈለቀ ፅፎ ያዘጋጀውን የ90 ደቂቃ ፊልም ለመስራት ሰባት ወራት የፈጀ ሲሆን አርቲስት ሜሮን ጌትነት፣ ተስፋ ብርሃኔ፣ ጣሊያናዊው ተዋናይና ጋዜጠኛ ግርሃም ማርሽ፣ ዳንኤል ታደሰ (ጋጋኖ)፣ ዮሐንስ ተፈራ፣ ሰለሞን ታሼ (ጋጋኖ) እና ሌሎች ኢትዮጵያውያን እና የውጭ ሀገር ዜጐች ተውነውበታል፡፡ ፊልሙን ደራሲ እና አዘጋጅ ከኢዮኤል አበራ ጋር ፕሮዱዩስ አድርገውታል፡፡
በሌላም በኩል ኢያሪኮ ማስታወቂያና ፊልም ፕሮዳክሸን “ቢንጐ” የተሰኘ ፊልም አቀረበ፡፡ ነገ የሚመረቀውን የ105 ደቂቃ ፊልም ፍቅሩ ፍሬው ፅፎ ያዘጋጀው ሲሆን ደረጀ ደመቀ፣ አልያስ ወሰንየለህ፣ ሚካኤል ታምሬ፣ ነብያት መኮንን፣ ዮሐንስ ተፈራ፣ ካሳሁን ፍስሃ (ማንኤላ) ወይንሸት በላቸው፣ ኒና መለሰ፣ ብርሃን ክፍሌ፣ ቤተልሄም ታዬ እና ሌሎችም ተውነውበታል፡፡ ፊልሙ የሚመረቀው በአዲስ አበባ እና በክልሎች በሚገኙ ሲኒማ ቤቶች ነው፡፡