ፀሐፊው ላለፉት ስምንት አመታት በፌደራል ሀገር ውስጥ ገቢ ባለሥልጣን እና በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን በታክስ ባለሙያነት አገልግለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና የሕግ እና የብድር ማገገሚያ ባለሙያ ናቸው፡፡
በሁሉም አለበል የተዘጋጁ አስር አጫጭር ልቦለዶች የተካተቱበት “የተዋጡ ነፍሶች” መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ በሁሉም አለበል የተፃፈው 201 ገፆች ያሉት መፅሐፍ ዋጋ 30 ብር ነው፡፡በሌላም በኩል በሕግ ባለሙያ አቶ ሳሙኤል ታደሰ የተዘጋጀው “ተጨማሪ እሴት ታክስ በኢትዮጵያ” መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ በርእሰ ጉዳዩ ዙርያ ባለ አስራ ሁለት ክፍል ትንታኔ የተሰጠበት መፅሐፍ፤ 288 ገፆች ያሉት ሲሆን ዋጋውም 60 ብር ነው፡፡
ፀሐፊው ላለፉት ስምንት አመታት በፌደራል ሀገር ውስጥ ገቢ ባለሥልጣን እና በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን በታክስ ባለሙያነት አገልግለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና የሕግ እና የብድር ማገገሚያ ባለሙያ ናቸው፡፡