Saturday, 22 February 2020 10:42

አሜሪካ “በራሪ ጠመንጃ” ለመስራት ማቀዷ ተነገረ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

     የአሜሪካ መከላከያ ቢሮ ፔንታጎን በ13.27 ሚሊዮን ዶላር በአይነቱ አዲስ የሆነና “ገንስሊንገር” የሚል ስያሜ የተሰጠው ዘመናዊ በራሪ ጠመንጃ ለመስራት ማቀዱ ተነግሯል፡፡
የአሜሪካ የወታደራዊ ፕሮጀክቶች ተቋም ዳርፓ ተግባራዊ ሊያደርገው ያቀደው አዲሱ በራሪ ጠመንጃ ያለ ተኳሽ በአየር ላይና በምድር እየበረረ ጥቃት መፈጸም የሚችል መሆኑን የዘገበው ፎክስ ኒውስ፤ ለአዲሱ ጠመንጃ ምርምርና ምርት የሚውለው ገንዘብ እንዲመደብለት መጠየቁን አመልክቷል፡፡
አዲሱ በራሪ ጠመንጃ ምን ያህል መጠን እንዳለውና የሚጠቀመው ተተኳሽ ምን እንደሆነ በግልጽ አለመታወቁን የጠቆመው ዘገባው፤ ሰርጎገቦችን ለማጥቃት በሚደረጉ ዘመቻዎች ላይ ጥቅም ላይ እንደሚውልም አመልክቷል፡፡

Read 1674 times