Print this page
Saturday, 18 January 2020 12:39

ከሰኔ 15 የባለሥልጣናት ግድያ ጋር በተያያዘ የተከሰሱት ጉዳያቸው በፕላዝማ እንዲታይ ተወሰነ

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(0 votes)

   ከሰኔ 15 የባለስልጣናት ግድያ ጋር በተያያዘ ክስ የተመሰረተባቸው እነ 10 አለቃ መሣፍንት ጥጋቡና ክርስቲያን ታደለ፤ ከእንግዲህ ጉዳያቸውን የሚከታተሉት በችሎት ቀርበው ሳይሆን ባሉበት ማረሚያ ቤት ሆነው በፕላዝማ እንዲሆን ፍ/ቤቱ ወሰነ፡፡
ባለፈው ታህሳስ 21 ቀን 2012 ዓ.ም በነበራቸው ቀጠሮ ወቅት በፍ/ቤቱ ግቢ ውስጥ ተቃውሞ መፈጠሩን ተከትሎ ፍ/ቤቱ ችሎት እየታወከ መሆኑን በመግለጽ ከእንግዲህ ጉዳያቸው የሚታየው ባሉበት ቦታ ሆነው በፕላዝማ እንዲሆን መወሰኑን አስታውቋል፡፡
ቀደም ባለው ችሎት ተከሳሾች ከማረሚያ ቤት አያያዝ፣ፖሊስ ጋ ያለ ንብረት ከመመለስ ጋር ተያይዞ ባቀረቧቸው አቤቱታዎች የሚመለከታቸውን አካላት ምላሽ ለመስማት እንዲሁም በ1ኛ ተከሳሽ 10 አለቃ መሣፍንት ጥጋቡ ላይ ተሻሽሎ የቀረበውን ክስ ለማዳመጥ ለትናንት ጥር 8 ቀን ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም ተከሳሾች ከነበሩበት ተሽከርካሪ ወርደው በችሎቱ ለመታደም ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ተከትሎ ፍ/ቤቱ ጉዳዩን መርምሮ ውሣኔውን ሊያሳልፍ ችሏል፡፡
በማረሚያ ቤትና በፖሊስ ምላሽ ላይ ብይን ለመስጠት እንዲሁም 1ኛ ተከሳሽ ላይ የቀረበውን የክስ ማሻሻያ ለማዳመጥና የቀሪ ተከሳሾችን የእምነት ክህደት ቃል ለመቀበል ፍ/ቤቱ ለየካቲት 18 ቀን 2012 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

Read 1014 times