Saturday, 04 January 2020 14:57

ረቡዕ በአለም ዙሪያ 392 ሺ ልጆች እንደተወለዱ ይገመታል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   የፈረንጆች አዲስ አመት የመጀመሪያዋ ቀን በሆነችው ባለፈው ረቡዕ ብቻ በመላው አለም 392 ሺህ ያህል ልጆች ተወልደዋል ተብሎ እንደሚገመት ተመድ አስታውቋል፡፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህጻናት መርጃ ተቋም ዩኒሴፍ ይፋ ያደረገውን መረጃ ጠቅሶ አልጀዚራ አንደዘገበው፤ በዕለቱ በህንድ 67 ሺህ 385፣ በቻይና 46 ሺህ 299፣ በናይጀሪያ 26 ሺህ 39 ህጻናት እንደተወለዱ ይገመታል፡፡
ባለፉት ሶስት አስርት አመታት ዕድሜያቸው አምስት አመት ሳይሞላቸው ለሞት የሚዳረጉ ህጻናት ቁጥር ከግማሽ በላይ መቀነስ  ቢያሳይም፣ የሚወለዱ ህጻናት ቁጥር በአንጻሩ በአዝጋሚነት መቀነሱን ተቋሙ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
በመላው አለም በፈረንጆች አመት 2018 በተወለዱ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የሞቱ ህጻናት ቁጥር 2.5 ሚሊዮን እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው.፤ ከእነዚህ መካከልም ከ35 በመቶ በላይ የሚሆኑት በተወለዱበት እለት ይህቺን አለም በሞት እንደተለዩዋትም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1989 times