Print this page
Saturday, 28 December 2019 13:51

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

        የኛ ፖለቲካ

ያኔ የልጅነቱን የምታስታውሱ
የሰፈሬ ልጆች ባካችሁ ተነሱ፡፡
ያ! የሰፈራችን
በልጅነታችን
ያልሾምነው መሪያችን
ያ! ጉልቤ አውራችን፡፡
“አለቃ ነኝ” ብሎ ራሱን የሰየመ
“ተቧቀሱ” ሚለን ትእዛዝ እየሰጠ
“ሆያ ሆዬ” ሲደርስ ገንዘብ ያዥ ሚሆነው
ከሱ የተረፈውን የሚያከፋፍለው
…ዝርዝሩ ብዙ ነው፡፡
ያ! የሰፈራችን
በልጅነታችን
ያ! ጉልቤ አውራችን፤
አሁን ልጆች ወልዶ ቤት ሰርቶ ይኖራል፤
ያደረሰውን “ግፍ” ረስቶትም ይሆናል፡፡
የወጋ ቢረሳ የተወጋ አይረሳ፤
ኑ! ቤቱን እናፍርስ ተነሱ እንነሳ፡፡
ስልጣኔ እና ፍቅር
እንደ ቀድሞ አይደለም
እንደጥንት አይደለም
እኩልነት መጥቷል፡፡
መናገር ማውራቱ
ለባል ብቻ አይደለም
ለሚስትም ተፈቅዷል፡፡
እንደ ቀድሞ አይደለም
እንደ ጥንት አይደለም
ስልጣኔ መጥቷል
እቤት ብቻ አይደለም
በስልክም ይወራል፡፡
እናም እኔና አንቺ
እቤት በእኩልነት
ስንርቅ በስልክ ቤት ብዙ እናወራለን
ግና ለመግባባት ምን ያህል ጠቀመን?
(የግጥም መድብል)
አንድነት ግርማ


Read 3105 times
Administrator

Latest from Administrator