Print this page
Saturday, 21 December 2019 13:21

የዝነኛ ሴቶች ጥግ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

• ‹‹በአገሪቱ ድንቅ የጥበብ ታሪክ ውስጥ የራሴን አሻራ ማስቀመጥ በሚያስችለኝ የሙያ መስክ መሰማራት በመቻሌ፣ ራሴን እንደ ዕድለኛ ነው የምቆጥረው፡፡…››
   ሳራ አበራ (ፋሽን ዲዛይነር)
• ‹‹ለአገሬ ትልልቅ ህልሞች አሉኝ:: ዴሞክራሲ እንዲሁ ለአፍ ያህል ብቻ የ ምናወራለት ሳ ይሆን ት ርጉም ያለው የሕይወታችን ዘይቤ እንዲሆን እፈልጋለሁ::››
   ሶፊ ይልማ (ጋዜጠኛና ፖለቲከኛ)
• ‹‹ለስኬቴ ምስጢሩ ለሥራዬ ያለኝ ከፍተኛ ፍቅር ነው፡፡ ሥራዬ ለእኔ ሕይወቴና በጋለ ውስጣዊ ፍቅር የምተጋለት ሁሉ ነገሬም ነው፡፡››
   ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ (አምባሳደር)
• ‹‹ከህክምና ዶክተሮች የላቀ ገቢ የሚያገኙ የጫማ ዲዛይን ሰሪዎች፣ ከባንክ ተቆጣጣሪዎች የበለጠ የሚከፈላቸው የስፌት ሠራተኞች በሶልሬብልስ ውስጥ
መኖራቸው ያኮራኛል፡፡ ብልፅግና ይሏል ይሄ ነው!››
   ቤተልሔም ጥላሁን (የሶልሬብልስ መሥራች)
• ‹‹ወደ ውስጣችሁ ተመልከቱ፤ በሕይወታችሁ ልትሰሩ ስለምትችሉት ታላቅ ነገር ራሳችሁን ጠይቁ፤ እናም አድርጉት!››
   ብሩክታዊት ጥጋቡ (የሕጻናት ቴሌቪዥን ፕሮግራም ፈጣሪ)
• ‹‹እያንዳንዷን ነገር በጥልቀት እንደ መፈተሽና ውስጣዊ ባህርያቱን እንደማወቅ የሚያጓጓ ነገር የለም፡፡››
   ዶ/ር ታደለች አቶምሳ (የፊዚክስ ባለሙያ፤ ተመራማሪ)
• ‹‹በኢትዮጵያ የትኛዋም ሴት ከጥቃት ነፃ አይደለችም ብዬ አምናለሁ፡፡ የፆታ ጥቃት ባይሆን እንኳን የሞራል ጥቃት አይቀርላትም፡፡››
    ወንጌል ተስፋዬ (ረዳት ሳጂን፤ ወንጀል መርማሪ)
(ከ‹‹ተምሳሌት - ዕፁብ ድንቅ ኢትዮጵያውያን ሴቶች›› የተወሰደ

Read 1420 times
Administrator

Latest from Administrator