Saturday, 07 December 2019 13:05

ማን ምን አለ?

Written by 
Rate this item
(0 votes)

(ስለ ኢትዮጵያ)
- ሞዴሊንግ የጀመርኩት ኢትዮጵያ ውስጥ ነው፤ ምክንያቱም ያደግሁት እዚያ ነው:: ት/ቤት በሚዘጋጅ የ ፋሽን ትርኢት ላይ በመስራት ነው የጀመርኩት፤ ሙያው ደስ ይለኝ ስለነበር በዚያው ገፋሁበት፡፡
   ሊያ ከበደ (ሞዴል)
- የኢትዮጵያ የልጅነት ትውስታ የለኝም:: ወደ ኒውዮርክ ተሻግሬ፣ ከኢትዮጵያ ማህበረሰብ አባላት ጋር መገናኘት እስክቀላቀል ድረስ ስለ ኢትዮጵያ ባህል ምንም አላውቅም ነበር፡፡
   ማርከስ ሳሙኤልሰን (ትውልደ - ኢትዮጵያዊ ሼፍ)
- አሜሪካን ከቬትናም ወይም ከኢትዮጵያ ለይቼ የማያት አይመስለኝም፡፡ ይሄ “የኛ ቡድን ከአንተ ቡድን ይሻላል” ይሉት ቅኝት - የተማሪ ሀሳብ ነው፡፡ ልጆቼ እንዲህ ያሉ የልዩነት መስመሮች አይገባቸውም፡፡ እኔም እንዲገባኝ አልሻም፡፡
    ብራድ ፒት (የፊልም ተዋናይ)
- አገሬ ሁልጊዜ በቁርጠኝነትና በጀግንነት እንደምታሸንፍ ዓለም እንዲያውቅ እፈልጋለሁ፡፡
    አበበ ቢቂላ (የማራቶን ጀግና)
- በኢትዮጵያ መልከ ጥፉ ሰዎች አላየሁም:: ኦፕራ ዊንፍሬይ
    (አሜሪካዊት የቶክ ሾው አዘጋጅ)
- ኢትዮጵያ የድሮው ዓይነት የሙስና ችግር አልነበራትም፡፡ የአፍሪካ መሪዎች በኛ ይቀኑ ነበር፡፡
    ኮሎኔል መንግስቱ ኃ/ማርያም (የቀድሞ ፕሬዚዳንት)
- ለኢትዮጵያ መሮጥ ብፈልግ እንኳን መንግስት ወይም ፌደሬሽን ይመርጡኛል ብዬ አልጠብቅም፡፡
    ፈይሳ ሌሊሳ (አትሌት)
- እንግሊዝ ራሷን እንደ ሰለጠነ አገር እንደምትቆጥር አውቃለሁ፤ ለእኔ ግን በብዙ መንገድ ኢትዮጵያ በእጅጉ ስልጡን አገር ትመስለኛለች፡፡
    ዶ/ር ካትሪን ሃምሊን (በኢትዮጵያ የፌስቱላ ሆስፒታል መስራች)

Read 1284 times