Saturday, 23 June 2012 08:11

ካናን አዲስ አልበሙን ከወር በኋላ ይለቃል

Written by  መልካሙ ተክሌ (melkamutekele@gmail.com)
Rate this item
(0 votes)

ካናን ከጦርነት ጠበሳ ይልቅ በልብ ውስጥ ያለ ትኩሳትን መዝፈን እፈልጋለሁ ሲል ለሲኤን ኤን ተናገረ፡፡ አስቀድሞ በእርስ በእርስ ጦርነት ስለታመሰችው ሶማሊያ እና ስለስደት ህይወቱ አብዝቶ ይዘፍን የነበረው ከናን ከወር በኋላ በሚወጣ አዲስ አልበሙ በግሉ ህይወቱ እና የፍቅር ሁኔታው ላይ የሚያተኩሩ ዘፈኖችን እንደሰራ ታውቋል፡፡

የ34 ዓመቱ ሶማሊያዊ ገጣሚና ሙዚቀኛ በሙሉ ስሙ ኬይናን አብዲ ዋርሴሜ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ከወር በኋላ ለገበያ የሚያበቃውን አዲስ አልበሙን‹ካንትሪ፤ ጎድ ኦር ዘ ገርል› ብሎ ሰይሞታል፡፡ በዚህ አዲስ የካናን አልበም ላይ ናስ ሞስ ዴፍ፤ ኔሊ ፎርታዶና ዊልአይአም አብረው ሰርተዋል፡፡

 

 

 

Read 924 times Last modified on Saturday, 23 June 2012 08:13