Saturday, 30 November 2019 12:36

የታንዛኒያ ገዢ ፓርቲ፣ በምርጫ 99.9 በመቶ ማሸነፉን እንግሊዝና አሜሪካ ተቃወሙ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    በታንዛኒያ ባለፈው እሁድ በተከናወነው አገራዊ ምርጫ፣ ገዢው ፓርቲ 99.9 በመቶ ድምጽ አግኝቶ ማሸነፉን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ፣ እንግሊዝና አሜሪካ ምርጫውን መቃወማቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
የሁለቱ አገራት አምባሳደሮች ባለፈው ማክሰኞ ባወጡት መግለጫ፤ በታንዛኒያ ስምንት ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ባልተሳተፉበት ሁኔታ የተካሄደውና መንበረ ስልጣኑን የተቆጣጠረው ቻማ ቻ ማፒንዱዚ ፓርቲ፣ 99.9 በመቶ ማሸነፉን ያወጀበት ምርጫ ተቃዋሚዎችን ያገለለ፣ ታዛቢዎች እንዳይሰማሩ የተደረጉበትና ብዙ ጉድለቶች የነበሩበት መሆኑ የምርጫውን ውጤት ጥያቄ ውስጥ ይጥለዋል ሲሉ መተቸታቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡
በምርጫው ለመወዳደር በዕጩነት ከቀረቡት የአገሪቱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ተወዳዳሪዎች መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት፣ በቅድመ ምርጫ ሰነዶች ላይ የቃላት ግድፈት ፈጽመዋል በሚሉና ሌሎች ተልካሻ ምክንያቶች በምርጫ ቦርድ ከእጩነት መባረራቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ ይህም የምርጫውን ውጤት ጥያቄ ውስጥ እንደከተተው ጠቁሟል፡፡

Read 10152 times