Saturday, 23 November 2019 17:39

የአዲስ አድማሱ ጋዜጠኛ መንግስቱ አበበ አረፈ

Written by 
Rate this item
(9 votes)

 የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ መንግስቱ አበበ ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ፣ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡
ጋዜጠኛ መንግስቱ፤ የአዲስ አድማስ የንግድና ኢኮኖሚ አዘጋጅ በመሆን፣ ከ15 ዓመት በላይ በትጋትና በታታሪነት የሰራ ብርቱ ጋዜጠኛ ነበር፡፡ በጋዜጣው ላይ በሰራባቸው ዓመታት  ከ300 በላይ ታዋቂ የንግድ ሰዎችን የስኬት ታሪክ፣ ባማረ አቀራረብና በማራኪ ቋንቋ፣ ለአዲስ አድማስ አንባቢያን በማቅረብ፣ ሥራ ፈጣሪነትንና ኢንቨስትመንትን በማበረታት ረገድ ጉልህ አገራዊ ሚና ተጫውቷል፡፡ ጋዜጠኛው ለሙያውና ለሥራው ባለው ፍቅር፣  እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ፣ በህመም ላይ ሳለ ጭምር፣ ከሥራው አልተለየም ነበር፡፡
ጋዜጠኛ መንግስቱ፤ በአዲስ ዘመንና በዕለታዊ አዲስ ጋዜጦችም ላይ  ለበርካታ ዓመታት በጋዜጠኝነት ማገልገሉ ይታወቃል፡፡  
የጋዜጠኛ መንግስቱ አበበ የቀብር ሥነ ሥርዓት በነገው ዕለት፣ ከቀኑ በ9 ሰዓት በቀጨኔ መድሃኒያለም ቤ/ክርስቲያን እንደሚከናወን ቤተሰቦቹ ለአዲስ አድማስ ገልጸዋል፡፡
የአዲስ አድማስ ዝግጅት ክፍልና ማኔጅመንት፣ በጋዜጠኛ መንግስቱ አበበ ዜና ዕረፍት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን እየገለጸ፣ ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን ይመኛል፡፡
 ፈጣሪ  ነፍሱን በአጸደ ገነት ያኑርልን፡፡     

Read 11228 times