Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 23 June 2012 07:15

30ኛው ኦሎምፒያድ ሶሻል ኦሎምፒክ ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ከወር በኋላ በለንደን አስተናጋጅነት የሚጀመረው 30ኛው ኦሎምፒያድ በሶሻል ሚዲያዎች በሚኖረው ሽፋን፤ በኦሎምፒክ ታሪክ አዲስ  ምእራፍ ይከፍታል ተባለ፡፡ ለንደን የምታስተናግደው ኦሎምፒክ እስከ140 ቃላትን በሚያስተናግዱ የሶሻል ሚዲያ መድረኮች ሽፋን ማግኘቱ በውድድሩ ታሪክ የመጀመርያው ከመባሉም በላይ ሶሻልኦሎምፒክ የሚል ስያሜን ያተረፈ ሆኗል፡፡

30ኛው ኦሎምፒያድ በዩቲውብ የቀጥታ ስርጭት እንደሚኖረው ዓለም አቀፉ የኦሎምፒክ ኮሚቴ ያስታወቀ ሲሆን ውድድሩ በተለይ በሁለቱ የሶሻል ሚዲያ ገፆች ፌስቡክ እና ትዊተር ከዓለም ዙርያ በርካታ ስፖርት አፍቃሪዎችን በማሳተፍ ልዩ ድምቀት እንዲኖረው ታስቧል፡፡ ከ4 ዓመታት በፊት ቤጂንግ ያስተናገደችው 29ኛው ኦሎምፒያድ በትዊተር 6 ሚሊዮን በፌስቡክ ደግሞ 100 ሚሊዮን ስፖርት አፍቃሪዎች እንደተከታተሉት ሲታወስ ለንደን የምታስተናግደው 30ኛው ኦሎምፒያድ 140 ሚሊዮን የትዊተር መልክቶችን እንዲሁም ከ900 ሚሊዮን በላይ የፌስቡክ ግንኙነቶችን በመፍጠር አዲስ ክብረወሰን ይኖረዋል በሚል ተጠብቋል፡፡ ዓለም አቀፉ የኦሎምፒክ ኮሚቴ በትዊተር ገፁ 760ሺ ተከታታዮች በፌስቡክ ደግሞ 2.8 ሚሊዮን ታዳሚዎች እንዳሉት ሲያስታውቅ በኦሎምፒክ መንደር በሚሰጠው ሽፋን አትሌቶችንና መላውን የዓለም ስፖርት አፍቃሪ በልዩ ልዩ የመረጃ ልውውጦች ለማርካት ዝግጅቱን በማጧጧፍ ላይ ነው፡፡ ባለፈው ሰኞ የፌስቡክ ኩባንያ ልዩ የኦሎምፒክ ገፅ የከፈተ ሲሆን ይህ መድረክ በኦሎምፒኩ ተሳታፊ የሆኑ 60 አገራትና 200 አትሌቶቻቸው ከሚጠቀሙት የፌስቡክ አድራሻ ጋር ግንኙነት ፈጥሮ የሚሰራ ይሆናል፡፡

 

 

 

 

Read 2193 times Last modified on Saturday, 23 June 2012 10:50