Print this page
Saturday, 09 November 2019 11:27

የዚምባቡዌ መንግስት 77 ሃኪሞችን ከሥራ አባረረ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

   የዚምባቡዌ መንግስት፣በቂ ደመወዝ አይሰጠንም በሚል የአገሪቱ የመንግስት ሰራተኞች በጀመሩት የስራ ማቆም አድማ ላይ ተሳትፈዋል ያላቸውን 77 የህክምና ዶክተሮች ከስራ ያባረረ ሲሆን ይህን ተከትሎም በርካታ የመንግስት ሰራተኞች ባለፈው ረቡዕ አደባባይ ወጥተው በፕሬዚዳንቱ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ማሰማታቸውን  ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
የአገሪቱ የመንግስት ሰራተኞች “የሚከፈለን ደመወዝ ከኑሮ ውድነቱ ጋር የማይመጣጠን በመሆኑ የደመወዝ ጭማሪ ሊደረግልን ይገባል” በሚል የስራ ማቆም አድማውን ማድረግ የጀመሩት ባለፈው መስከረም ወር እንደነበር ያስታወሰው ቢቢሲ፤ ፍርድ ቤት “የስራ ማቆም አድማው ህገ ወጥ በመሆኑ በ48 ሰዓታት ውስጥ ወደ ስራ ገበታችሁ እንድትመለሱ” የሚል ትዕዛዝ ቢያስተላልፍም፣ ከስራ የተባረሩት 77 ሃኪሞች ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል ብሏል፡፡
በዚምባቡዌ የስራ ማቆም አድማውን ያላቋረጡ ሌሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ የህክምና ዶክተሮች እንዳሉ የጠቆመው ዘገባው፤ መንግስት በእነሱም ላይ ተመሳሳይ እርምጃ ሊወስድ እንደሚችል ቢነገርም፣ይህን ማድረግ ክፉኛ የተጎዳውን የአገሪቱን የህክምና ዘርፍ የባሰ ቀውስ ውስጥ ያስገባዋል የሚል ስጋት መፈጠሩን አመልክቷል፡፡
በኢኮኖሚ ቀውስና በዋጋ ግሽበት በተመታችው ዚምባቡዌ፣ የዜጎች ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ መምጣቱንና የመንግስት ሰራተኞችን ጨምሮ ብዙዎች ኑሯቸውን መምራት የማይችሉበት ፈታኝ ሁኔታ ውስጥ መግባታቸውን ያስታወቀው ዘገባው፤ የአንድ የህክምና ዶክተር ወርሃዊ ደመወዝም ከ100 ዶላር በታች መውረዱንና በዚህም ሳቢያ በርካታ ሃኪሞች ስራቸውን በመልቀቃቸው የጤና ተቋማት፣ ስራ እስከማቆም ደረጃ መድረሳቸውን ጠቁሟል፡፡

Read 1949 times
Administrator

Latest from Administrator