Print this page
Saturday, 19 October 2019 14:05

ፖሊስ ወንጀልን በ2 ቀናት ውስጥ እንዲያጠፋ ሙሴቬኒ አዘዙ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዮሪ ሙሴቬኒ፣ የአገሪቱ ፖሊስ በከተሞች እየተስፋፋ ያለውን የወንጀል ድርጊት በ2 ቀናት ውስጥ እንዲያጠፋ መመሪያ መስጠታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
በአገሪቱ የተለያዩ ከተሞች ግድያና ዝርፊያን ጨምሮ የተለያዩ ወንጀሎች መስፋፋታቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ ጉዳዩ ያሳሰባቸው ፕሬዚዳንት ሙሴቬኒም፣ ፖሊስና የጸጥታ ሃይሎች በጋራ በመምከር በሁለት ቀናት ጊዜ ውስጥ ወንጀሎቹን ማስቆም የሚችሉበትን እቅድ በአፋጣኝ እንዲያቀርቡ ትዕዛዝ መስጠታቸውን አመልክቷል፡፡
ወንጀለኞችን በሙሉ በሁለት ቀናት ውስጥ ማጥፋት ይቻላል ብለው እንደሚያምኑ የተናገሩት ሙሴቬኒ፤ ዜጎች በወንጀለኞች ሲዘረፉና ሲገደሉ እያዩ ዝም የሚሉበት ጊዜ እንዳበቃ ገልጸዋል፡፡
በአገሪቱ መኖሪያ ቤቶችንና ድርጅቶችን ሰብረው እየገቡ በገጀራና በሌሎች መሳሪያዎች እያስፈራሩ ዝርፊያ የሚፈጽሙ በቡድን የተደራጁ ወጣቶች እየተበራከቱ መምጣታቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ እጅግ በርካታ ዜጎች በወንጀለኞቹ ቢዘረፉና ቢገደሉም የአገሪቱ ፖሊስ ይህ ነው የሚባል እርምጃ ሳይወስድ በመቆየቱ ሲወቀስ እንደነበርም አስታውሷል፡፡


Read 1308 times
Administrator

Latest from Administrator