Print this page
Saturday, 19 October 2019 13:56

ሁዋዌ ገቢው በ24 በመቶ ማደጉን አስታወቀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ከአሜሪካ መንግስት የተጣለበት ማዕቀብ ክፉኛ ያንኮታኩተዋል ተብሎ ተሰግቶለት የነበረው የቻይናው የሞባይል አምራች ኩባንያ ሁዋዌ፣ ያለፉት ዘጠኝ ወራት ገቢው በ24 በመቶ ማደጉን አስታውቋል፡፡
ሁዋዌ ኩባንያ ሰሞኑን ያወጣውን መግለጫ ጠቅሶ ብሉምበርግ እንደዘገበው፣ ኩባንያው እስካለፈው መስከረም ወር በነበሩት ያለፉት ዘጠኝ ወራት 185 ሚሊዮን የሞባይል ስልኮቹን ለአለማቀፍ ገበያ በማቅረብ 86.1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝቷል፡፡
ሁዋዌ ከሞባይል ሽያጭ በተጨማሪ እጅግ ፈጣኑን የ5ጂ ኔትወርክ በስራ ላይ ለማዋል የሚያግዙ የቴሌኮም መሳሪያዎችን ለመሸጥ 60 ያህል የሽያጭ ስምምነቶችን በአለም ዙሪያ ከሚገኙ ኩባንያዎች ጋር መፈጸሙን የጠቆመው ዘገባው፤ ያም ሆኖ ግን የአሜሪካ ማዕቀብ የኩባንያውን አጠቃላይ አመታዊ ገቢ ክፉኛ ይጎዳዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክቷል፡፡
ሁዋዌ ባለፈው አመት የአለማችን ሁለተኛው ግዙፍ የሞባይል አምራችነት ስፍራን ከአሜሪካው አፕል ኩባንያ መረከቡን ያስታወሰው ዘገባው፣ ተግቶ በመስራት የሳምሰንግን ቦታ በመረከብ የአለም ቁጥር አንድ የሞባይል አምራች ኩባንያ የመሆን ግብ ቢያስቀምጥም፣ የአሜሪካ ማዕቀብ ግቡን እንዳይመታ እንቅፋት ይፈጥርበታል ተብሎ እንደሚጠበቅ አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1242 times
Administrator

Latest from Administrator