Print this page
Saturday, 19 October 2019 12:55

የግዮን መጽሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር ለፍርድ ተቀጠረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የግዮን መጽሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር የሆነው ፍቃዱ ማህተም ወርቅ ከ6 ዓመት በፊት ያሳትመው ከነበረው እንቁ መጽሔት ጋር በተያያዘ በቀረበበት የወንጀል ክስ ጉዳይ ማክሰኞ ለፍርድ ተቀጥሯል፡፡ በ2006 ዓ.ም ነሐሴ ወር መንግስት ሕገ መንግስቱን በሃይል የመናድ ተግባር ላይ ተሰማርተዋል በሚል ክስ ከመሰረተባቸው 5 መጽሔቶች እና 1 ጋዜጣ መካከል አንዱ የነበረው የእንቁ መጽሔት በወቅቱ ከግብር ጋር በተያያዘም ተጨማሪ ክስ ቀርቦበት እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡ በወቅቱ ክስ ቀርቦባቸው ከነበሩ መጽሔቶች ጋዜጦች በርካቶቹ በፍ/ቤት ውሳኔ የተዘጉ ሲሆን ይህን ተከትሎም ከ40 በላይ ጋዜጠኞች በወቅቱ
ከአገር መሰደዳቸውም ይታወሳል፡፡ በወቅቱ ከአገር እንዳይወጣ እግድ ተጥሎበት የነበረው የእንቁ መጽሔት ተወካይ የነበረው ፍቃዱ ማህተመ ወርቅ ላለፉት አመታት በገቢዎች የቀረበበትን ክስ ሲከታተል መቆየቱን ለአዲስ አድማስ አስታውቆ ለመጨረሻው የፍርድ ውሳኔ ከ6 ዓመት በኋላ ለማክሰኞ ጥቅምት 11 ቀን 2012 እንደሰጠው ቀጠሮ እንደተሰጠው አስታውቋል፡፡ በአገሪቱ ለውጥ ከመጣ በኋላ ክሱ አግባብነት የሌለው መሆኑን ለማስረዳት ላለፈው 1 ኣመት ለጠቅላይ አቃቤ ሕግና ለሚመከታቸው ሁሉ ለማስረዳት መሞከሩን የገለፀው ፍቃዱ ነገር ግን እስከ ዛሬ ቀና ምላሽ አለማግኘቱን አስረድቷል፡፡ እንቁ መጽሔት በወንጀልና ከታክስ ጋር በተያያዘ በተከፈተበት ክስና መዋከብ ህትመቷ እንዲቋረጥ ከተደረገ በኋላ ፍቃዱ ማህተም ወርቅ ‹‹ጊዮን›› ሳምንታዊ መጽሔትን መስርቶ እየሰራ መሆኑም ይታወቃል፡፡

Read 7157 times
Administrator

Latest from Administrator