Saturday, 16 June 2012 12:41

“ማዳጋስካር 3” በ3ዲ ለዐይታ ቀረበ

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(0 votes)

ባለፈው ሳምንት በ3ዲ በሰሜን አሜሪካ ለዕይታ የበቃው “ማዳጋስካር 3፡ ዩሮፕ ሞስት ዋንትድ” የተሰኘው አስቂኝ አኒሜሽን ፊልም የሰሜን አሜሪካ የቦክስ ኦፊስ ሳምንታዊ ገቢ ደረጃን ተቆጣጠረ -60.4 ሚሊዮን ዶላር በማስገባት፡፡ “ማዳጋስካር 3”በካኔስ የፊልም ፌስቲቫል ከተመረቀ በኋላ ባለፉት ሁለትሳምንታት በመላው ዓለም ሲታይ የቆየ ሲሆን አጠቃላይ ገቢውም 135.9 ሚሊዮን ዶላር መድረሱ ታውቋል፡፡ በሪድሊ ስኮት ዲያሬክት የተደረገው “ፕሮሜትየስ” የተሰኘ ሳይንሳዊ ልቦለድ ፊልም ደግሞ 50 ሚሊዮን ዶላር ሁለተኛ ደረጃን ይዟል - በቦክስ ኦፊስ፡፡

“ማዳጋስካር 3” ምርጥ የቤተሰብ ፊልም መሆኑን የጠቆመው ሎስአንጀለስ ታይምስ፤ ፊልሙ በ145ሚ.ዶላር በጀት እንደተሰራ አመልክቷል፡፡ በፊልሙ ላይ ቤን ስቴለር፤ ክሪስ ሮክ፤ ጃዳ ፒንኬት ስሚዝ እና ዴቪድ ስኩዊመር በድምጽ ሲተውኑ እስከ 5ሚ.ዶላ እንደተከፈላቸው ታውቋል፡፡ፊልሙ በአጠቃላይ ከ500 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ሊያስገኝ እንደሚችልም ተገምቷል፡፡ ከሰባት ዓመት በፊት በ78 ሚሊዮን ዶላር የተሰራው የፊልሙ የመጀመርያው ክፍል 532.68 ሚሊዮን ዶላር ሲያስገባ፤  ከአራት ዓመት በፊት በ150 ሚሊዮን ዶላር በጀት የተሰራው ሁለተኛው ክፍል 604 ሚሊዮን ዶላር አስገብቷል፡፡

 

 

Read 685 times Last modified on Saturday, 16 June 2012 12:43