Tuesday, 08 October 2019 09:33

“የረሃብ አድማ” - አዲሱ የትግል ስትራቴጂ?

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የምርጫ ቦርድ ያወጣው አዲሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች አዋጅ “ህልውናችንን” አደጋ ላይ ይጥላል” ብለው የሰጉ ኢህአፓና መኢአድን ጨምሮ 70 ተቃዋሚ ፓርቲዎች (ወይስ ተፎካካሪ?)፤ ህጉ የማይሻሻል ከሆነ ለሁለት ቀናት የረሃብ አድማ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል (እንኳንም ከሁለት ቀን በላይ አልሆነ!)
በነገራችን ላይ ለፓርቲ ምስረታ የ10ሺ ሰዎች ፊርማ ማሰባሰብ የሚጠይቀውን የህጉን ድንጋጌ  መሰለኝ አጥብቀው የተቃወሙት፡፡ ልብ አድርጉ! የ10ሺ ሰዎች ፊርማ ማሰባሰብ ዳገት የሆነባቸው ፓርቲዎች፣ በምርጫ ተወዳድረው በለስ ከቀናቸው ከ100 ሚ በላይ ህዝብ ነው የሚመሩት፡፡ ግን 10ሺ ፊርማ ማሰባሰብ አልቻሉም፡፡ በረሃብ አድማው ወቅት ህዝቡ በፀሎት እንዳይለያቸው የጠየቁ መሰለኝ፡፡ ግን የትኛውን ህዝብ ማለታቸው ይሆን? (የ10ሺ ህዝብ ፊርማ ማሰባሰብ አልቻሉም እኮ!) ግን የተሻለ የፈጠራ ሃሳብ አጥተው ነው ረሃብን እንደ ትግል ስትራቴጂ የመረጡት? ነገሩን ማለቴ ነው እንጂ መብታቸው ነው፡፡
እኔ የምፈራው የሰብአዊ መብታችን ተጣሰ እንዳይሉ ብቻ ነው- በረሃብ አድማው!!
ሳሚ - ከመሃል
አዲስ አበባ   

Read 1163 times