የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር በየወሩ የሚያዘጋጀው ብሌን የኪነጥበብ ምሽት 8ኛው ዙር መርሃ ግብር “የዘመን ቀለማት” በሚል ርዕስ
የፊታችን ማክሰኞ ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር ይካሄዳል፡፡ በምሽቱ ሞሃዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት፣ ዶ/ር ምህረት ደበበ፣ ፀደቀ ይሁኔ (ኢ/ር)፣ ኮሜዲያን አዝመራው ሙሉሰው እንዲሁም ገጣሚያኑ አበረ አያሌው፣ ልዑል ሀይሌ፣ በቃሉ ሙሉና ማህሌት አፈወርቅ ሥራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን መግቢያ በነፃ መሆኑ ታውቋል፡፡