ኡጋንዳዊው ተማሪ ብሎክ አድርገውኛል በሚል ፕሬዚዳንቱን ከሷቸዋል
የቀድሞው የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ናጂብ ራዛቅ፣ ከ4.5 ቢሊዮን ዶላር በላይ የህዝብ ገንዘብ በሙስና በመመዝበር ለግል ጥቅማቸው አውለዋል በሚል በተመሰረተባቸውና በአለማችን ግዙፉ የሙስና ቅሌት እንደሆነ በተነገረለት የሙስና ክስ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡
ናጂብ ራዛቅ በስልጣን ዘመናቸው የመዘበሩትን የህዝብ ገንዘብ እጅግ ዘመናዊ የአሜሪካ የቅንጦት ቤቶችን ከመግዛት አንስቶ ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ከሚገባው በላይ ለማቀናጣት ተጠቅመውበታል መባሉን የዘገበው ዘ ጋርዲያን፤በአጠቃላይ 25 ክሶች እንደተመሰረቱባቸውና ሁሉንም ክሶች ክደው እንደተከራከሩ አመልክቷል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ በቫርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርቱን በመከታተል ላይ የሚገኘው ኡጋንዳዊው ወጣት ቴለር ሴጉያ፣ በትዊተር ገጹ ላይ አምባገነን ብሎ ስለጠራቸው ብቻ ብሎክ ያደረጉትን የአገሪቱን ፕሬዚዳንት ዮሪ ሙሴቬኒን በፍርድ ቤት መክሰሱ ተዘግቧል፡፡
ወጣቱ በሙሴቬኒ ላይ በመሰረተው ክስ፣ ሀሳቤን በነጻነት የመግለጽና የመወያየት መብቴን ጥሰዋልና ቅጣት ይገባቸዋል ማለቱን የጠቆመው ዘገባው፤ በመዲናዋ ካምፓላ የሚገኘው ፍርድ ቤት ጉዳዩን እየመረመረው እንደሚገኝም አመልክቷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል