Monday, 26 August 2019 00:00

የወቅቱ መልዕክት

Written by 
Rate this item
(3 votes)


        “--ችግርን እንደ ንሥር ከላዩ ሆነን ስናየው ግን ቀልሎና ኢምንት ሆኖ ይታየናል። ልንንደው፣ ልናስወግደው እንደምንችል እናምናለን። ከከፍታ
ወርደን ታች ለመድረስ ቁልቁለቱ ይቀለናል፣ ያንን የወረድነውን መልሰን መውጣት ግን ዳገት ይሆንብናል። ሆኖም የት እንደነበርን ማስታወስ
ከዳገቱ የበለጠ አቅም እንዳለን እንድንረዳ ያደርጋል። የወረድነውን ዳገት መልሰን መውጣት ብቻም ሳይሆን ከዚያም በላይ ከፍ ማለት እንደምንችል እንድንረዳ ያደርገናል። ለዚህ ነው ችግርን ለማስተካከል ከመነሣታችን በፊት አስቀድመን ችግሩን የምናይበትን ቦታ ማስተካከል የሚያስፈልገን።
ማረግ የሚያስፈልገንም ለዚህ ነው።-ችግሮቻችንን ከበላያቸው ሆነን ለማየት እንድንችል። ኢትዮጵያን ተብትበው የያዟት አያሌ ችግሮች ሊፈቱና እስከ መጨረሻው ሊወገዱ እንደሚችሉ የሚያምኑም የማያምኑም አሉ። የሁለቱ ልዩነት ካገኙት መረጃና ካካበቱት ዕውቀት የሚመጣ አይደለም። ከቆሙበት ቦታ የሚመነጭ ነው። እንደ አሸንዳ /ሻደይ/አሸንድዬ/ ሶለል፤ ወጣት ሴቶች ለማረግ የወሰኑ፣ ችግሮቹን ከላያቸው ሆነው ያዩዋቸዋል። ራሳቸውንም ከችግሮቹ በላይ ያገኙታል። እንደ እነዚህ ወጣት ሴቶች ለዕርገት ያልተዘጋጁት ግን ራሳቸውን ከችግሮቹ ሥር ወድቀው ያገኙታል። ያኔ ተስፋ ይቆርጣሉ።--”
(ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ፤
ለአሸንዳ /ሻደይ/ አሸንድዬ/
ሶለል በዓል ካስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ
መልዕክት የተቀነጨበ፤ ነሐሴ 15 ቀን 2011 ዓ.ም)

Read 5492 times