ታሪክ ሰሪና ታሪክ ዘጋቢ አንድ ጊዜ በአገራችን አንድ ከፍተኛ ኮሚቴ ይቋቋማል፡፡ ይህ ኮሚቴ የኢትዮጵያን ታሪክ፣ ባህል፣ ሥነ ቃል ወዘተ… በማጥናት ስለ ሕዝቡ ሥነ ልቦናዊ ሁኔታ በቂ ግንዛቤ ለመጨበጥ እንዲቻል እንዲያደርግ ኃላፊነት የተሰጠው ነው፡፡ ከኮሚቴው አባላት መካከል አንደኛው ዶክተር የዩኒቨርሲቲ መምህር ሲሆን በጊዜው ከነበረው መንግስት የፖሊት ቢሮ አባላት ከአንደኛው ጋር የድሮ የት/ቤት ጓደኞች ናቸው፡፡ ይህንኑ የፖሊት ቢሮ አባል ለኮሚቴው ሥራ ኢንተርቪው ሊያደርገው ሄዶ ያገኘዋል፡፡ የፖሊት ቢሮው ባለሥልጣን፤ ከዶክተሩ ጋር ከረዥም ጊዜ በኋላ በመገናኘታቸው ተገርሞ፤ ‹‹ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? አንተ ወደኛ ግቢ (ቤተ-መንግስት ማለቴ ነው) እንድትመጣ የሚያደርግ ምን ሁኔታ ተፈጠረ?›› ሲል ይጠይቀዋል፡። ዶክተሩም ሲመልስ፤ ‹‹እኔም ገርሞኛል፤ አንተን ታሪክ ሰሪ፣ እኔን ታሪክ ዘጋቢ ያደረገን ጊዜ ነው!›› አለው፡፡ ታሪክ ዘጋቢ አያሳጣን!!
(አዲስ አድማስ፤ ሰኔ 1 ቀን 1994 ዓ.ም)
Published in
ባህል