መፃሕፍቱ እዚህ እስኪደርሱ አንድ አመት ፈጅቷል፡፡” ብለዋል፡፡ እነዚሁ መፃሕፍት የዶ/ር ሚካኤል ልጅ ሃና ሚካኤል ከሌሎች የክብር እንግዶች ጋር በተገኘችበት በመጪው ሐሙስ ርክክብ የሚደረግ ሲሆን የዩኒቨርስቲው አዲስ ቤተመፃሕፍት አንድ ክፍል በዶክተሩ እንደሚሰየም ለማወቅ ተችሏል፡፡
የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ባህል ጥናት ትምህርት ክፍል በእንግሊዝ ይኖሩ ከነበሩት ዶ/ር ሚካኤል ኢያሱ 2500 መፃሕፍትን በእርዳታ አገኘ፡፡ አሁን በሕይወት የሌሉት የኦክስፎርድ ዩንቨርሲቲ ምሩቅ ዶ/ር ሚካኤል ኢያሱ ከሰጧቸው መፃሕፍት አብዛኞቹ የፍልስፍና ናቸው፡፡ ለመፃሕፍቱ በእርዳታ መገኘት ምክንያት የሆኑት የዩኒቨርሲቲው ታሪክና ባህል ጥናት ድህረ ምረቃ አስተባባሪ ተባባሪ ፕሮፌሰር አየለ በከሬ ለአዲስ አድማስ በሰጡት ቃለ ምልልስ “መፃሕፍቱን ከእንግሊዝ ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ ከወጣው አራት ሺህ ፓውንድ እና ሀገር ውስጥ ከገባ በኋላ ለጉምሩክ የተከፈለውን ጨምሮ የመጋዘን ኪራይ 120ሺህ ብር ፈጅቶብናል፡፡
መፃሕፍቱ እዚህ እስኪደርሱ አንድ አመት ፈጅቷል፡፡” ብለዋል፡፡ እነዚሁ መፃሕፍት የዶ/ር ሚካኤል ልጅ ሃና ሚካኤል ከሌሎች የክብር እንግዶች ጋር በተገኘችበት በመጪው ሐሙስ ርክክብ የሚደረግ ሲሆን የዩኒቨርስቲው አዲስ ቤተመፃሕፍት አንድ ክፍል በዶክተሩ እንደሚሰየም ለማወቅ ተችሏል፡፡