Saturday, 27 July 2019 12:03

አቫታር የምንጊዜም ከፍተኛ ገቢ ክብረወሰኑን ተነጠቀ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 እ.ኤ.አ በ2009 ለእይታ የበቃውና የምንጊዜም ባለከፍተኛ ገቢ ፊልም ሆኖ የዘለቀው የጄምስ ካሜሮን ፊልም አቫታር፣ ባለፈው እሁድ በአቬንጀርስ ኢንድጌም ክብሩን መነጠቁን ሲኤንኤን ዘግቧል፡፡
ካሜሩን በ1998 ለእይታ ያበቃው ታይታኒክ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ በማግኘት ታሪክ መስራቱን ያስታወሰው ዘገባው፣ በ2010 በሌላኛው ተወዳጅ ፊልሙ አቫታር 2 ቢሊዮን ዶላር በማግኘት የራሱን ክብረወሰን መስበሩንና ባለፈው እሁድ ግን በአቬንጀርስ ኢንድጌም ክብሩን መነጠቁን አመልክቷል፡፡
ባለፈው ሚያዝያ ለእይታ የበቃው አቬንጀርስ ኢንድጌም በድምሩ 2.79 ቢሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት፣ በአለማችን የፊልም ታሪክ ከፍተኛውን ገቢ ያገኘ ፊልም ሆኖ ከመንበሩ ላይ መቀመጡንም ዘገባው አመልክቷል፡፡

Read 3708 times