የመጀመርያ አልበሙን ካወጣ 20 ዓመታት ያስቆጠረው አሸር “ሉኪንግ 4 ማይሰልፍ” የተሰኘ አዲስ አልበሙን የፊታችን ማክሰኞ ለገበያ ያበቃል፡፡ የአሸር አዲስ አልበም በአር ኤንድ ቢ እና በኤሌክትሮኒክ የሙዚቃ ስልቶች የተሰሩ 14 ዘፈኖችን ይዟል፡፡ ከሮይተርስ ጋር ባደረገው ቃለምልልስ አዲሱን አልበም በተዋበ ጥበብ መስራቱን የገለፀው አሸር፤ ዳግም የተወለድኩበት ስራ ነው ብሏል፡፡ ማይክል ጃክሰን በዳንስ ተምሳሌቴ እንደሆነው ሁሉ በፈጠራ የታዋቂው ሰዓሊ ፒካሶ የጥበብ ስራዎች አነቃቅተውኛል ሲልም ተናግሯል፡፡ አሸር አዲስ አልበሙን ለገበያ በሚያበቃበት እለት በለንደን ከተማ በሚገኘው የሃመርስሚዝ አፖሎ ቲያትር የሚያቀርበውን ኮንሰርት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተሰሩ የሆሎግራም ዳንሰኞችን በመጠቀም፣ በዩቲውብ ድረገፅ የቀጥታ ስርጭት እንደሚኖረው ተጠቁሟል፡፡ በአልበም ምረቃ አዲስ አቅጣጫ ያሳያል የተባለው የአሸር አልበም በ youtube.com/UsherVEVO ላይ አድናቂዎቹ የራሳቸውን ምስል እንደአቫታር በመፍጠር አብረው እየደነሱ የሙዚቃ ድግሱን እንዲሳተፉበት ያስችላል እየተባለ ነው፡፡