በሎሬት ዶ/ር ተወልደብርሃን ገ/እግዚብሔር የህይወት ታሪክ እና ስራ ላይ ያተኮረውና በዘነበ ወላ የተፃፈው “የምድራችን ጀግና” መጽሐፍ ማክሰኞ ሐምሌ 16 ቀን 2011 ዓ.ም ከቀኑ 11 ሰዓት ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ይመረቃል፡፡
በምረቃ ስነ ሥርዓቱ ላይ ሎሬቱ እና የቀድሞ ተማሪዎች፣ ወዳጆች እና የስራ ባልደረቦችን ጨምሮ ታዋቂ ገጣሚያንና ደራሲያን ይገኛሉ ተብሏል፡፡ ዶ/ር በድሉ ዋቅራ፣ ኤፍሬም ስዩምና ዶ/ር ሱራፌል ወንድሙ በእለቱ የግጥም ስራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ የምርቃቱ አዘጋጅ አዳነ መታሰቢያ የማስታወቂያ ስራ ድርጅት አስታውቋል፡፡
Saturday, 20 July 2019 12:10
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና