Monday, 15 July 2019 10:44

የሰሜን ኮርያው መሪ ከዩኒቨርሲቲ በማዕረግ ተመረቁ መባሉ እያነጋገረ ነው

Written by 
Rate this item
(2 votes)


            የሰሜን ኮርያው ፕሬዚዳንት ኪም ጁንግ ኡን፣ ከታዋቂው የአገሪቱ የውትድርና ዩኒቨርሲቲ በማዕረግ መመረቃቸው መዘገቡን ተከትሎ ፕሬዚዳንቱ አንድም ቀን ትምህርታቸውን በቅጡ ተከታትለው እንደማያውቁ እርግጠኞች ነን የሚሉ ውስጥ አዋቂዎች ጉዳዩን መሳለቂያ እንዳደረጉት ቢዝነስ ኢንሳይደር ዘግቧል፡፡
ኪም ጁንግ ኡን በአያታቸው ስም ከተሰየመው ታላቁ የኪም ኢ ሱንግ የውትድርና ዩኒቨርሲቲ በማዕረግ መመረቃቸውን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን በስፋት መዘገባቸውን የጠቆመው ቢዝነስ ኢንሳይደር፤ አንዳንድ ውስጥ አዋቂዎች ግን “ወደ ዩኒቨርሲቲው ግቢ ድርሽ ብሎ አያውቅም፤ እንደለመደው ዝና ፍለጋ ያስወራው ወሬ ነው” በማለት ፕሬዚዳንቱን መተቸታቸውን አመልክቷል፡፡
ፕሬዚዳንቱ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ መማራቸውን የሚያሳይ ምንም አይነት የፎቶግራፍ፣ የጽሁፍም ሆነ የሰነድ ማስረጃ እንደሌለ የተናገሩት አንድ የአገሪቱ የቀድሞ የጦር ሃይል አባል፤ “እንኳን በማዕረግ ሊመረቁ ዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ ገብተው አያውቁም” ሲሉ የምርቃት ዜናውን ማጣጣላቸውን ዘገባው ገልጧል፡፡

Read 2828 times