ማጣርያ አካሂጃለሁ ያለው ብሮድካስት ባለሥልጣንም ተመጣጣኝ የአየር ሰዓት መድቦ በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቅ ለዚህም የሽልማት አዘጋጆችና ዳኞች አስተያየት መካተት እንዳለበትና የማስተባበያ ፕሮግራሙ በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን ውሳኔ መሠራቱም ጭምር እንዲገለፅ እንዲሁም ፕሮግራሙ ከግንቦት 16 ጀምሮ በሚቆጠር 15 ቀናት ውስጥ እንዲቀርብ ባለሥልጣኑ ወስኗል፡፡ አቅራቢዎቹ በዝግጅት ወቅት ለስህተትና ሕግ ጥሰት አቅራቢዎችንና አድማጮችን ይቅርታ እንዲጠይቁ እና አፈፃፀሙንም ዝግጅታቸውን ባቀረቡ በሦስት ቀናት ለባለሥልጣኑ እንዲያሳውቁ አዟል፡፡ “ብራና” የሚል በንባብ ባህል ላይ የሚሠራ ዝግጅት በኤፍኤም 97.1 እሁድ በተመሳሳይ ሰዓት የሚተላለፍ ዝግጅት ያለው እናት የማስታወቂያ ሥራዎች ድርጅት በቅርቡ ለንባብ መጎልበት አግዛችኋል በማለት ደራስያንን፣ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማትንና ሌሎችን መሸለሙ ይታወቃል፡፡