Monday, 10 June 2019 11:40

ሙምባይ በትራፊክ መጨናነቅ ከአለም 1ኛ ሆናለች

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 የህንዷ ከተማ ሙምባይ ባለፈው የፈረንጆች አመት 2018 ከአለማችን አገራት ከተሞች መካከል እጅግ አስከፊው የትራፊክ መጨናነቅ ችግር የነበረባት ቀዳሚዋ ከተማ መሆኗን አንድ አለማቀፍ ጥናት አመለከተ፡፡
ቶምቶም የተባለው የሆላንድ የጥናት ተቋም በ56 የአለማችን አገራት ውስጥ በሚገኙ 403 ከተሞች ላይ የሰራውን ጥናት ጠቅሶ ሲኤንኤን እንደዘገበው፣ በሙምባይ ጎዳናዎች ላይ የሚያሽከረክር አንድ ሾፌር በትራፊክ መጨናነቅ ሳቢያ ጉዞው ከሚፈጅበት ጊዜ 65 በመቶ ያህል ተጨማሪ ጊዜ ለማባከን ተገድዷል፡፡
የኮሎምቢያዋ መዲና ቦጎታ በትራፊክ መጨናነቅ ከአለማችን ከተሞች በሁለተኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ የጠቆመው ዘገባው፣ በከተማዋ ጎዳናዎች የሚመላለሱ መኪኖች ካሰቡበት ለመድረስ 57 በመቶ ተጨማሪ ጊዜ እንደሚፈጅባቸውም አመልክቷል:: በትራፊክ መጨናነቅ የፔሩዋ ሊማ በሶስተኛ፣ የህንዷ ርዕሰ መዲና ኒው ደልሂ በአራተኛ ደረጃ ላይ መቀመጣቸውን የጠቀሰው ተቋሙ፤ ባለፉት አስር አመታት 75 በመቶ በሚሆኑት የአለማችን ከተሞች የትራፊክ መጨናነቅ ችግር ተባብሶ ቀጥሏል ብሏል፡፡

Read 6596 times