Saturday, 02 June 2012 10:36

ስታሎን አክሽን ፊልሞች እየጠፉ ናቸው አለ

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(0 votes)

ዘመናዊ የሱፕር ሂሮ ፊልሞች አክሽን ፊልሞችን እያጠፉ መሆናቸውን የፊልም ባለሙያው ሲልቨስተር ስታሎን ተናገረ፡፡ ከ20 እና 30 አመት በፊት ተወዳጅ የነበሩ ጡንቸኛ የፊልም ገፀባህርያት ዛሬ በፊልም ተመልካቾች አይፈለጉም ያለው የሮኪና የራምቦ ፊልሞች ተዋናይ ስታሎን፤የተለያዩ የልዕለ ተፈጥሮ ባህርይ ያላቸው ፍጡራንና ጀብደኛ ገፀባህርያት የሲኒማ ኢንዱስትሪውን ተቆጣጥረውታል ሲል ለኢንተርቴይመንት ዊክሊ በምሬት ተናግሯል፡፡

በሌላ በኩል የሆሊውድ ትልልቅ የአክሽን ተዋናዮችን ያሰባሰበበው “ዘ ኤክስፐንደብልስ” የተባለው አክሽን ፊልም ክፍል 2 ከሁለት ወር በኋላ ለእይታ ይበቃል፡፡ በፊልሙ ላይ ሲልቨስተር ስታሎን፤ ጄሰን ስታታም፤ጄት ሊ፤ ዶልፍላንድ ግሪን፤ አርኖልድ ሸዋዚንገር፤ ብሩስ ዊልስና   ጂን ክላውድ ቫንዳም እንደሚተውኑ ታውቋል፡፡ በሲልቨስተር ስታሎንና በአሮንልድ ሽዋዚንገር ጥምረት የሚተወነው ሌላው የአክሽን ፊልም “ዘ ቶምብ” በቀረፃ ላይ እንደሆነም ተገልፃል፡፡ዘንድሮ በሆሊውድ ተሰርተው ለገበያ የቀረቡ የአክሽን ፊልሞች 570 እንደሚደርሱ የገለፀው ቦክስ ኦፊስ ሞጆ፤ከ1990 ጀምሮ ባሉት 22 ዓመታት ከአክሽን ፊልሞች የተገኘው ገቢ 33 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን ጠቁሞ፤ አክሽን ፊልም ከኮሜዲ፤አድቬንቸርና ድራማ ፊልሞች ቀጥሎ በአራተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ይገልፃል፡፡

 

 

Read 1894 times Last modified on Saturday, 02 June 2012 10:41