Saturday, 18 May 2019 00:00

ከ”የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ” የተሰጠ ማስተባበያ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)


                 አዲስ አድማስ ጋዜጣ ቅዳሜ ግንቦት 3 ቀን 2011 ዓ.ም ባወጣው ዕትሙ፣ “የልብ ማዕከሉ ይፈተሽ” በሚል ርዕስ ስር ያቀረበው ፅሑፍ፤ ለአገርና ለወገን ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ የሚገኘውን የልብ ህክምና ማዕከሉን ስራና ተግባር የሚያጎድፍ፣ እውነታን የማይገልጽና ማስረጃ የሌለው ተራ ወቀሳ ነው፡፡ በጋዜጣው ላይ በዶ/ር በላይ አበጋዝ ተተክተው የተቀመጡት ከሙያው ጋር ግንኙነት የሌላቸው “…የሂሳብ ሰራተኛ፣ የቦርድ ዋና ሰብሳቢ፣ የማዕከሉ ዋና አስተዳደርና የሰው ኃይል ኃላፊ እንዲሁም የፋይናንስ ኃላፊ ሆነው እየሰሩ ይገኛሉ፡፡
ይህን ሁሉ ኃላፊነት ጠቅልለው መያዛቸው የልብ ማዕከሉ ከእርሳቸው ውጪ ኃላፊና ለምን ብሎ ጠያቁ እንዳይኖረው እያደረገ ሲሆን ማዕከሉን ለዝርፊያና ለብክነት አጋልጦታል” በማለት የተጠቀሰው ሐሰት ነው፡፡ ማዕከሉ በፅሁፍ እንደተገለፀው ሳይሆን የራሱ ሜዲካል ዳይሬክተር፣ የሂሳብ ባለሙያ፣ የፋይናንስ ኃላፊና ሥራ አስኪያጅ ያለው ነው፡፡ አወቃቀሩም ቢሆን ህግንና ደንብን የተከተለ፣ ግልፅ አሰራር ያለው ነው፡፡ ይሁን እንጂ ጋዜጣው የፀሐፊውን የአንድ ወገን መሰረተ ቢስ ፅሑፍ ተቀብሎ፣ ከማዕከሉ በኩል ያለውን እውነታ ሳያካትት፣ ከፍተኛ የስም ማጥፋት ዘመቻ ከፍቶብናል፡፡
ያለ በቂ ምክንያት ልምድ ያላቸው ሰራተኞች በኃላፊው ተሰናብተዋል የተባለውም፣ ማን እንደተሰናበተና ለምን እንደተሰናበተ ሳይገልጽ፣ በደፈናው የቀረበ መሰረተ ቢስ ውንጀላ ነው፡፡
ሰላሃዲን ከሊፋ
የበኢ.ል.ሕ.ሕ.መ ቦርድ ሰብሳቢ
ማህተምና ፊርማ አለው

Read 1163 times Last modified on Monday, 20 May 2019 10:32