Monday, 13 May 2019 00:00

“ሰላምና እርቅን በማስፈን የአብያተ ክርስቲያናት ሚና” በሚል ውይይት ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማህበር፤ ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ተጨባጭ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት “ሠላምና እርቅን በማስፈን የአብያተ ክርስቲያናት ሚና” በሚል ርዕስ የምክክር ጉባኤ ማዘጋጀቱን አስታወቀ፡፡
ግንቦት 10 ቀን 2011 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በአፍሪካ ህብረት ዋና ጽ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ በሚከናወነው በዚህ ጉባኤ ላይ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የሃይማኖት መሪዎችና ከመላው ኢትዮጵያ የተውጣጡ የማህበረሰብ ክፍሎች፣ እንዲሁም መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት መሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል ተብሏል፡፡
በዚህ መሰረት፤ “በሠላምና እርቅ ተግባር ላይ የሀይማኖት ተቋማት ሚና” በሚል ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ፣ “ትውልድን በሰላምና በእርቅ የማሳተፍ ተግባር” በሚል ወ/ሮ ሰላማዊት ቸርነት እንዲሁም “የዘረኝነት ገጽታ በማህበረሰብ ዕድገትና በሀገር ሰላም ላይ ያስከተለው ተፅዕኖ” በሚል አቡነጴጥሮስ ጥናታዊ ጽሑፎች የሚያቀርቡ ሲሆን የመፍትሔ አቅጣጫዎችና እቅዶችን በመንደፍ ጉባኤው እንደሚጠናቀቅ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 9746 times